የ2026 የዓለም ዋንጫ ዕጣ ድልድል በዋሽንግተን ዲሲ ይከናወናል
አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 16፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ የ2026 የዓለም ዋንጫ ዕጣ ድልድል በፈረንጆቹ ታህሳስ 5 ቀን 2025 በዋሽንግተን ዲሲ ይከናወናል አሉ።
ፕሬዚዳንቱ ይህንን ሲያስታውቁ የዓለም አቀፉ የእግር ኳስ ፌዴሬሽኖች ማህበር (ፊፋ) ፕሬዚዳንት ጂያኒ ኢንፋቲኖ እና የአሜሪካው ምክትል ፕሬዚዳንት ጄዲ ቫንስ ተገኝተዋል።
የዕጣ ድልድሉ ዋሽንግተን ዲሲ በሚገኘው የኬኔዲ ማዕከል እንደሚደረግ ማስታወቃቸውን ዘ አትሌቲክ ዘግቧል፡፡
የ2026ቱ የዓለም ዋንጫ በአሜሪካ፣ ሜክሲኮ እና ካናዳ ጣምራ አስተናጋጅነት የሚካሄድ ሲሆን የ48 ሀገራት የእግርኳስ ብሔራዊ ቡድኖች በመድረኩ ይሳተፋሉ፡፡
በሚኪያስ አየለ
ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation
Facebook www.facebook.com/fanabroadcasting
Telegram t.me/fanatelevision
Website www.fanamc.com
TikTok www.tiktok.com/@fana_television
WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29
Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment
Facebook www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate
TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment
Amharic Podcast YouTube www.youtube.com/@fanamcpodcast በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!