Fana: At a Speed of Life!

ሕዳሴ ግድብ የመቻላችን ልኬት፤ የአንድነታችን ማሕተም ነው – አቶ አወሉ አብዲ

አዲስ አበባ፣ መስከረም 6፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የመቻላችን ልኬት፤ የአንድነታችን ማሕተም ነው አሉ የኦሮሚያ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አወሉ አብዲ።

የሕዳሴ ግድብ በስኬት ተጠናቅቆ መመረቁን በማስመልከት በአሰላ ከተማ የፓናል ውይይት እየተካሄደ ይገኛል።

በፓናል ውይይቱ ላይ አቶ አወሉ አብዲ እንዳሉት፤ የሕዳሴ ግድብ ከፍፃሜው እንዲደርስ ብዙ መስዋዕትነት ተከፍሏል።

የግንባታ ሂደቱ በውስብስብ ችግሮች ውስጥ ወድቆ እንደነበር አስታውሰው፤ ይህንን በማረም ግድቡ በተሳካ ሁኔታ እንዲጠናቀቅ ተደርጓል ብለዋል።

ግድቡ የላብ፣ የደም እና የዕምባ ውጤት ያሉት አቶ አወሉ፤ ይህም ትልቅ ትርጉም ያለው የመቻላችን ልኬት፣ የአንድነታችን ማሕተም ነው ሲሉ ተናግረዋል።

ሕዳሴ በአንድነት እና በሕብረት ሁሉም እንደሚቻል ህብረተሰቡ ያሳየበት እንደሆነ ገልጸው፤ ግንባታው ለፍፃሜ እንዲበቃ ሕዝቡ ላደረገው ያልተቆጠበ ድጋፍ አመስግነዋል።

በወንድሙ አዱኛ

ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation
Facebook www.facebook.com/fanabroadcasting
Telegram t.me/fanatelevision
Website www.fanamc.com
TikTok www.tiktok.com/@fana_television
WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29
Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment
Facebook www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate
TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment
Amharic Podcast YouTube www.youtube.com/@fanamcpodcast በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.