Fana: At a Speed of Life!

የፋና ላምሮት 5ኛው የአሸናፊዎች አሸናፊ የፍፃሜ ውድድር ዛሬ ይካሄዳል

አዲስ አበባ፣ መስከረም 10፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ለሥስት ወራት በብርቱ ፉክክር ሲካሄድ የቆየው የፋና ላምሮት 5ኛው የአሸናፊዎች አሸናፊ የፍፃሜ ውድድር በዛሬው ዕለት በድምቀት ይካሄዳል።

በውድድሩ ለፍጻሜ የበቁት ጴጥሮስ ማስረሻ፣ እየሩሳሌም አሰፋ፣ እዮቤል ፀጋዬ እና ኤፍሬም ጌታቸው ብርቱ ፉክክር ይጠብቃቸዋል።

የዕለት አቀራረብ ላይ መሰረት በማድረግ በዳኞች እና በተመልካቾች ድምፅ የውድድሩ አሸናፊ የሚለይ ሲሆን፤ በውድድሩ አንድ እንግዳ በክብር ዳኛነት ይገኛል።

በ13ኛው ሳምንት አራት ምርጥ ተወዳዳሪዎችን ይዞ የፍፃሜ ውድድሩን የሚያካሂደው ፋና ላምሮት 5ኛው የአሸናፊዎች አሸናፊ ውድድር ከ3 ነጥብ 3 ሚሊየን ብር በላይ ሽልማት የተዘጋጀለት ሲሆን፤ የዋንጫ እና የአዲስ ሙዚቃ ሽልማት ያበረክታል።

ይህን ደማቅ ውድድር በቀጥታ ስርጭት ከቀኑ 6:00 ጀምሮ በፋና ሚዲያ ኮርፖሬሽን ሁሉም የሚዲያ አማራጮች ይከታተሉ።

ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation
Facebook FBC (Fana Broadcasting Corporate S.C.)
Telegram t.me/fanatelevision
Website www.fanamc.com
TikTok www.tiktok.com/@fana_television
WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29
Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment
Facebook WMCC
TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment
Amharic Podcast YouTube www.youtube.com/@fanamcpodcast በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.