ሕዳሴ ግድብ የኢትዮጵያውያንን የዘመናት ቁጭት የመለሰ ነው – ከንቲባ ከድር ጁሃር
አዲስ አበባ፣ መስከረም 12፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የኢትዮጵያውያንን የዘመናት ቁጭት የመለሰ ነው አሉ የድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ከድር ጁሃር ።
የሕዳሴ ግድብ መጠናቀቁን አስመልክቶ በድሬዳዋ ከተማ ስቴዲየም የድጋፍ እና የደስታ መግለጫ ሰልፍ ተካሂዷል፡፡
ከንቲባ ከድር በዚህ ወቅት እንዳሉት÷ የሕዳሴ ግድብ በመላ ኢትዮጵያውያን ትብብር እና አንድነት እውን የሆነ ዳግማዊ ዓድዋ ነው ብለዋል፡፡
የሕዳሴ ግድብ ለሌሎች የአፍሪካ ሀገራት ጭምር የኢኮኖሚ ነጻነት ማረጋገጥ እንደሚቻል ብርሃን ያሳየ መሆኑን ጠቅሰዋል፡፡
በፕሮጀክቱ ግንባታ የታየውን የኢትዮጵያውያን ትብብር በቀጣይ በሌሎች ሀገራዊ ፕሮጀክቶች ላይ መድገም እንደሚገባም አመልክተዋል፡፡
ሕዳሴ ግድብ በሀገር ውስጥ የሃይል ተደራሽነትን ከማሳደግ ባለፈ የቀጣናውን የሃይል ትስስር እንደሚያጠናክርም ተናግረዋል፡፡
ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation
Facebook FBC (Fana Broadcasting Corporate S.C.)
Telegram t.me/fanatelevision
Website www.fanamc.com
TikTok www.tiktok.com/@fana_television
WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29
Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment
Facebook WMCC
TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment
Amharic Podcast YouTube www.youtube.com/@fanamcpodcast በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!