Fana: At a Speed of Life!

የኮይሻ ኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት ከባለፈው ጉብኝት በኋላ የሚለካ የሥራ እድገት አሳይቷል – ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር)

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 12፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የኮይሻ የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት ባለፈው ከነበረኝ ጉብኝት በኋላ የሚለካ የሥራ እድገት ታይቶበታል አሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማሕበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት መረጃ÷ ዛሬ የ2018 ዓ.ም የመጀመሪያ 100 ቀናት የማክሮ ኢኮኖሚ አፈፃፀም ግምገማ የጀመርነው የኮይሻ የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት በመጎብኝት ነው ብለዋል።

ፕሮጀክቱ ባለፈው ከነበረኝ ጉብኝት በኋላ የሚለካ የሥራ እድገት ታይቶበታል ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር)÷ የግድቡ ከፍታ 128 ሜትር መድረሱን ተናግረዋል።

አጠቃላይ የሲቪል ሥራውም 70 ከመቶ መድረሱን ገልጸዋል።

ይህ ስኬት ለኃይል ምንጭ ዋስትናችን ላለን ያላሰለሰ ጽኑ ጥረት ምስክር የሚሆን ነው ሲሉም አጽንዖት ሰጥተዋል።

ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation
Facebook www.facebook.com/fanabroadcasting
Telegram t.me/fanatelevision
Website www.fanamc.com
TikTok www.tiktok.com/@fana_television
WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29
Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment
Facebook www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate
TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment
Amharic Podcast YouTube www.youtube.com/@fanamcpodcast በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.