Fana: At a Speed of Life!

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ታላሚ ተኮር የማካካሻ ክትባት …

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 13፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ዕድሜያቸው ከአምስት ዓመት በታች ለሆኑ ሕጻናት ታላሚ ተኮር የተቀናጀ ማካካሻ ክትባት በዘመቻ እየተሰጠ ነው።

በክልሉ ጤና ቢሮ የእናቶች እና ሕጻናት ጤናና ሥርዓተ ምግብ አገልግሎት ዳይሬክተር አቶ ተስፋዬ ሌጂሶ ለፋና ዲጂታል እንዳሉት ፥ የክትባት ዘመቻው ለተከታታይ 10 ቀናት ይሰጣል።

በዚህም ባለፉት 5 ዓመታት በተለያዩ ምክንያቶች ክትባት ያልጀመሩ 101 ሺህ 417፣ ጀምረው ያቋረጡ 93 ሺህ 695 እንዲሁም የኩፍኝ ክትባት ያልተከተቡ 193 ሺህ 309 ሕጻናት ክትባቱን እንደሚወስዱ ተናግረዋል።

በዘመቻው በርቀትና መልክዓምድር ምክንያት ክትባት ያልወሰዱ፣ በከተሞች ውስጥ በጎዳና እና በከተማ ዳርቻ የሚገኙ ሕጻናትን በማፈላለግ ክትባት እንደሚሰጥ አብራርተዋል፡፡

ከክትባቱ ጎን ለጎንም የሥርዓተ ምግብ ልየታ፣ የማሕጸን ውልቃት፣ የፊስቱላ እና የማሕጸን በር ካንሰር ሕመም ያለባቸው የሕብረተሰብ ክፍሎችን የመለየት ሥራ እንደሚከናወን አመልክተዋል፡፡

በአድማሱ አራጋው

ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation
Facebook www.facebook.com/fanabroadcasting
Telegram t.me/fanatelevision
Website www.fanamc.com
TikTok www.tiktok.com/@fana_television
WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29
Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment
Facebook www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate
TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment
Amharic Podcast YouTube www.youtube.com/@fanamcpodcast በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.