የብልፅግና ፓርቲ ከፍተኛ አመራሮች ስልጠና እየተካሄደ ነው
አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 20፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የብልፅግና ፓርቲ የ2018 ዓመታዊ የከፍተኛ አመራሮች ስልጠና መካሄድ ጀምሯል።
ስልጠናው “በመደመር መንግሥት እይታ፣ የዘርፎች እምርታ” በሚል መሪ ሃሳብ ለሚቀጥሉት 10 ተከታታይ ቀናት እንደሚሰጥ ተመላክቷል፡፡
ስልጠናው የአመራሩን እውቀት፣ ክህሎትና አቅም የሚገነቡ ልዩ ልዩ ርዕሰ ጉዳዮች የሚቀርቡበት ነው።
በስልጠናው ከ2000 በላይ ከፌዴራልና ከክልል የተወጣጡ ከፍተኛ አመራሮች ተሳትፈዋል፡፡
ከስልጠናው በተጓዳኝ የተግባር የመስክ የልማት ሥራ ጉብኝቶች የሚካሄድ ይሆናል።