Fana: At a Speed of Life!

በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ 3.95 በማምጣት የወርቅ ሜዳልያ ተሸላሚዋ ዶ/ር ሜሮን ለገሰ

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 5፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ዶክተር ሜሮን ለገሰ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ሕክምና ት/ቤት 3.95 አማካይ ውጤት በማምጣት የከፍተኛ ውጤትና የወርቅ ሜዳልያ ተሸላሚ ሆናለች፡፡

አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በዛሬው ዕለት በተለያዩ የሕክምና ዘርፎች ያሰለጠናቸውን 263 አዳዲስ ባለሙያዎችን አስመርቋል፡፡

ዶ/ር ሜሮን ለገሰ ከሕክምና ት/ቤት 3.95 አማካይ ውጤት በማምጣት የከፍተኛ ውጤት እና የወርቅ ሜዳልያ ተሸላሚ መሆን ችላለች፡፡

ዶ/ር ሜሮን በአሁኑ ወቅት በከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የሴት ተማሪዎች ውጤታማነትና ተሳትፎ እየተሻሻለ መምጣቱን ተናግራለች፡፡

በዘርፉ ያገኘችውን እውቀት ለሀገሯና ለወገኖቿ በቅንነት ለማገልገል ዝግጁ እንደሆነች መግለጿንም የዩኒቨርሲቲው መረጃ ያመላክታል፡፡

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.