Fana: At a Speed of Life!

ፕሬዚዳንት ታዬ ከኦስትሪያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጋር ተወያዩ

አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 12፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀ ሥላሴ ከኦስትሪያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ቤአተ ሜይንል-ራይዚንገር ጋር ተወያይተዋል፡፡

በውይይታቸውም የኢትዮጵያ እና የኦስትሪያ የሁለትዮሽ ግንኙነትን ማጠናከር በሚያስችሉ ጉዳዮች ዙሪያ መክረዋል።

በተጨማሪም በጋራ ጉዳዮች ላይ በትብብር ለመስራት የሚያስችል ምክክር ማድረጋቸውን የፕሬዚዳንት ጽህፈት ቤት መረጃ አመላክቷል።

በሀገራቱ መካከል ረጅም ዘመናትን ያስቆጠረ ጠንካራ ግንኙነት ያለ ሲሆን፤ ትምህርት፣ ሳይንስና ኢኮኖሚን ጨምሮ በተለያዩ የልማት ትብብር መስኮች በአጋርነት ይሰራሉ።

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.