Fana: At a Speed of Life!

ጌዲዮን ጢሞቲዎስ (ዶ/ር) ከኖርዌይ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጋር ተወያዩ

አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 16፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቲዎስ (ዶ/ር) ከኖርዌይ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ኤስፒን ቤርዝ ጋር ተወያይተዋል፡፡

ጌዲዮን (ዶ/ር) በውይይቱ ወቅት ኢትዮጵያ እና ኖርዌይ ሊተባበሩባቸው የሚችሉባቸው ብዙ መስኮች እንዳሉ ገልጸዋል።

በኢትዮጵያ እና ኖርዌይ መካከል ዘርፈ ብዙ ትብብር ሊኖር እንደሚገባ ገልጸው÷ ግንኙነታቸውም ጠንካራ መሆኑን አንስተዋል፡፡

የሁለቱ ሀገራት ትብብር በንግድ፣ በኢንቨስትመንት እና በአካባቢ ጥበቃ ሊሰፋ እንደሚገባ አጽንኦት ሰጥተዋል፡፡

ኤስፒን ቤርዝ በበኩላቸው÷ የተለያዩ የኖርዌይ ኩባንያዎች በኢትዮጵያ ያለውን ዕድል መጠቀም ይፈልጋሉ ብለዋል።

ኢትዮጵያ የኮፕ32 አዘጋጅ በመሆኗ ሀገራቸው አስፈላጊውን ድጋፍ እንደምታደርግም ማረጋገጣቸውን የሚኒስቴሩ መረጃ አመልክቷል፡፡

ጌዲዮን ጢሞቲዎስ (ዶ/ር) በኦስሎ ቆይታቸው ከኖርዌይ የዓለም አቀፍ የልማት ትብብር ሚኒስትር፣ ከአየር ንብርትና አካባቢ ሚኒስትር፣ ከኢንቨስትመንት ፈንድ ዋና ዳይሬክተር፣ ከልማት ትብብር ኤጀንሲ ዋና ዳይሬክተር እና ከባለሃብቶች ጋር በትብብር ለመስራት በሚያስችሉ መስኮች ዙሪያ መክረዋል።

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.