ጌዲዮን ጢሞቲዎስ (ዶ/ር) ከኖርዌይ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጋር ተወያዩ
አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 16፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቲዎስ (ዶ/ር) ከኖርዌይ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ኤስፒን ቤርዝ ጋር ተወያይተዋል፡፡
ጌዲዮን (ዶ/ር) በውይይቱ ወቅት ኢትዮጵያ እና ኖርዌይ ሊተባበሩባቸው የሚችሉባቸው ብዙ መስኮች እንዳሉ ገልጸዋል።
በኢትዮጵያ እና ኖርዌይ መካከል ዘርፈ ብዙ ትብብር ሊኖር እንደሚገባ ገልጸው÷ ግንኙነታቸውም ጠንካራ መሆኑን አንስተዋል፡፡
የሁለቱ ሀገራት ትብብር በንግድ፣ በኢንቨስትመንት እና በአካባቢ ጥበቃ ሊሰፋ እንደሚገባ አጽንኦት ሰጥተዋል፡፡
ኤስፒን ቤርዝ በበኩላቸው÷ የተለያዩ የኖርዌይ ኩባንያዎች በኢትዮጵያ ያለውን ዕድል መጠቀም ይፈልጋሉ ብለዋል።
ኢትዮጵያ የኮፕ32 አዘጋጅ በመሆኗ ሀገራቸው አስፈላጊውን ድጋፍ እንደምታደርግም ማረጋገጣቸውን የሚኒስቴሩ መረጃ አመልክቷል፡፡
ጌዲዮን ጢሞቲዎስ (ዶ/ር) በኦስሎ ቆይታቸው ከኖርዌይ የዓለም አቀፍ የልማት ትብብር ሚኒስትር፣ ከአየር ንብርትና አካባቢ ሚኒስትር፣ ከኢንቨስትመንት ፈንድ ዋና ዳይሬክተር፣ ከልማት ትብብር ኤጀንሲ ዋና ዳይሬክተር እና ከባለሃብቶች ጋር በትብብር ለመስራት በሚያስችሉ መስኮች ዙሪያ መክረዋል።