ጌዲዮን ጢሞቲዎስ (ዶ/ር) ከደቡብ አፍሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጋር ተወያዩ
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 6፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቲዎስ (ዶ/ር) ከደቡብ አፍሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሮናልድ ላሞላ ጋር ተወያይተዋል፡፡
ሚኒስትሮቹ በሕንድ ኒው ዴልሂ እየተካሄደ ከሚገኘው የብሪክስ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች ጉባኤ ጎን ለጎን ባደረጉት ውይይት በሁለትዮሽ ጉዳዮች ላይ መክረዋል፡፡
በደቡብ አፍሪካ የሚገኙ ኢትዮጵያውያን ላይ ያነጣጠሩ ችግሮችን ለመፍታት በጋራ ለመስራት መስማማታቸውንም የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃ አመልክቷል፡፡