ነገ የሚጀመረውን ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ በስኬት ለማካሄድ የተሟላ ዝግጅት ተደርጓል
አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 7፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በነገው ዕለት የሚጀመረውን ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ በስኬት ለማካሄድ የተሟላ ዝግጅት ተደርጓል አሉ የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ዋና ኮሚሽነር መስፍን አርዓያ (ፕ/ር)፡፡
የመከላከያ ማርቺንግ ባንድ የሀገራዊ የምክክር ጉባኤውን ዋዜማ ምክንያት በማድረግ በአዲስ አበባ የተለያዩ አደባባዮችና ጎዳናዎች ደማቅ ትርዒት እያቀረበ ነው፡፡
መስፍን አርዓያ (ፕ/ር) በዚሁ ወቅት እንዳሉት፥ ኢትዮጵያ በታሪኳ ለመጀመሪያ ጊዜ ለምታካሄደው ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ አስፈላጊ ቅድመ ዝግጅቶች ተጠናቅቀው ዋዜማው ላይ እንገኛለን ብለዋል።
በዚህ ታሪካዊ ጉባኤ ላይ ከተለያዩ የሕብረተሰብ ክፍሎች የተወከሉ 4 ሺህ በላይ ታሳታፊዎች በጋራ በመቀመጥ በሀገራቸው የጋራ ጉዳዮች ላይ በሰፊው ይመክራሉ ብለዋል።
ሀገርን በጽኑ መሠረት ላይ ለመገንባት በሚደረገው በዚህ ታሪካዊ ጉባኤ እያንዳንዱ ተመካካሪ በንቃት እንዲሳተፍ ጥሪ ማቅረባቸውን ኢዜአ ዘግቧል፡