የከተማ አስተዳደሩ ከፍተኛ አመራሮች ከሩሲያ ዓለም አቀፍ የቢዝነስ ትብብር አባላት ጋር ተወያዩ
አዲስ አበባ፣ ጥር 25፣ 2013(ኤፍ ቢ ሲ) የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከፍተኛ አመራሮች ከሩሲያ ሴንት ፒተርስበርግ ከተማ ዓለም አቀፍ የቢዝነስ ትብብር አባላት ጋር ተወያዩ።
በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የመንግስት አገልግሎት ሰጪ ተቋማት አስተባባሪ አቶ ጃንጥራር አባይ እና ሌሎች የከተማ አስተዳደሩ ከፍተኛ አመራሮች÷ ከሩሲያ ሴንት ፒተርስበርግ ከተማ ከተውጣጡ የዓለም አቀፍ የቢዝነስ ትብብር አባላት ጋር በተለያዩ የንግድ እና ኢንቨስትመንት አማራጮች ዙሪያ ተወያይተዋል።
በተለይ አዲስ አበባ የአፍሪካ ህብረት መቀመጫ እና የተለያዩ ሀገራት ዲፕሎማቲክ መናኸሪያነቷ ባለፈ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ እያስመዘገበች ባለው እድገት በርካታ ጎብኚዎችን በመሳብ ላይ ያለች ከተማ መሆኗን የጠቀሱት አባላቱ በመንግስት እና በግል ዘርፍ ትብብር ላይ አብሮ ለመስራት ፍላጎት እንዳላቸው ገልጸዋል።
የከተማዋን እድገት በሚያፋጥኑ የቴክኖሎጂ ፣ የአገልግሎት፣ የንግድ እና ኢንቨስትመንት ዘርፎች ከከተማ አስተዳደሩ ጋር ለመስራት ያላቸውን የቢዝነስ አማራጮች ለከፍተኛ አመራሮቹ አብራርተዋል።
በአውሮፓ እና አፍሪካ ሀገራት ከ5 ቢሊየን ዶላር በላይ በተለያዩ የኢንቨስትመንት ዘርፎች መሰማራታቸውን አባላቱ ተናግረዋል፡፡
በውይይቱም አቶ ጃንጥራር አባይ የተለያዩ ኩባንያዎች በከተማዋ በተለይም በዘመናዊና አነስተኛ ዋጋ ባላቸው የመኖሪያ ቤቶች ግንባታ፣ በደረቅ ቆሻሻ አወጋገድ፣ በሳይንስና ቴክኖሎጂ በመሳሰሉት ቢሰማሩ ውጤታማ እንደሚሆኑ ገልፀውላቸዋል።
በውይይቱ የሚመለከታቸው የከተማዋ ቢሮ እንዲሁም የአዲስ ቻምበር ሃላፊዎች የተገኙ ሲሆን በጋራ ትግበራ ቡድን ወደ ተጨባጭ ኢንቨስትመንት መግባት በሚያስችል መልኩ ከስምምነት መደረሱን ከከተማ አስተዳደሩ ፕሬስ ሴክሬታሪያት ፅህፈት ቤት ያገኘነው መረጃ ያመላክታል።
ከፌስቡክ ገፃችን በተጨማሪ ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
የፋና ድረ ገጽ https://www.fanabc.com/ ይጎብኙ፤
ተንቀሳቃሽ ምስሎችን ለማግኘት የፋና ቴሌቪዥን የዩቲዩብ ቻናል https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/ ሰብስክራይብ ያድርጉ
ፈጣን መረጃዎችን ለማግኘት ትክክለኛውን የፋና ቴሌግራም ቻናል https://t.me/fanatelevision ይቀላቀሉ
ከዚህ በተጨማሪም በትዊተር ገጻችን https://twitter.com/fanatelevision ይወዳጁን
ዘወትር ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!