Fana: At a Speed of Life!

የሸገር ዳቦ ፋብሪካ ከዛሬ ጀምሮ በቀን 1 ነጥብ 5 ሚሊየን ዳቦ ያመርታል

አዲስ አበባ ፣ መጋቢት 7 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) ሸገር ዳቦ ፋብሪካ በሙሉ አቅሙ ወደ ማምረት ሊገባ ነው፡፡

በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ አዳነች አቤቤ የተመራ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎች ቡድን ፋብሪካ ያለበትን አጠቃላይ ሁኔታ ጎብኝቷል፡፡

በዚህ ወቅትም ምክትል ከንቲባ አዳነች አቤቤ ዳቦ ፋብሪካው በዚህ ሳምንት ሙሉ በሙሉ ወደ ማምረት እንደሚገባ ተናግረዋል፡፡

ለዚህም የከተማ አስተዳደሩ በወር 100 ሺህ ኩንታል ስንዴ እንደሚያቀርብም ነው የተናገሩት፡፡

የሜድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ አቶ ጀማል አህመድ ፋብሪካው በቀን 1 ነጥብ 5 ሚሊየን ዳቦ ማምረት ይጀምራል ብለዋል፡፡

በሙሃመድ አሊ

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.