Fana: At a Speed of Life!

በፕሬዚደንት ሣህለ ወርቅ ዘውዴ የሚመራዉ የዓለም ዓቀፉ የትምህርት ስርዐት ኮሚሽን ውይይት አካሄደ

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 8፣ 2013(ኤፍ ቢ ሲ)በፕሬዚደንት ሣህለ ወርቅ ዘውዴ የሚመራዉ የዓለም ዓቀፉ የትምህርት ስርዐት የወደፊት ሁኔታ ላይ ለመምከርና ለማቀድ የተቋቋመው ኮሚሽን ውይይት አካሂዷል፡፡

ኮሚሽኑ ሪፖርቱን ለማጠናቀቅ ከሁለተ ወር ያነሰ ጊዜ የቀረው ሲሆን፥ አባላቱ በሪፖርቱ ዝርዝር ይዘት ላይ የተወያዩበት ቁልፍ ስብሰባ መካሄዱን ከፕሬዚደንት ጽህፈት ቤት ያገኘነው መረጃ ያመለክታል፡፡

ኮሚሽኑ ከመላው ዓለም የተውጣጡ ታዋቂ ባለሙያዎችን ያቀፈ ሲሆን፥ ይፋዊ ክርክር፣ የፖሊሲ ውይይት ፣ የጋራ እርመጃዎችን የማያነሳሳ እና የትምህርት የወደፊት እጣ ፈንታ ምን መምሰል አለበት ለሚለዉ ዉይይት በር ከፋች የሚሆን ሪፖርት እያዘጋጀ ይገኛልም ነው የተባለው፡፡

ሪፖርቱ ለዩኔስኮ ጠቅላላ ጉባኤ በህዳር ወር 2021 ይቀርባል ተብሎ ይጠበቃል፡፡

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.