የሰላም ሚኒስትሯ ከተመድ የፖለቲካና ሰላም ግንባታ ጉዳዮች ዋና ፀሀፊ ጋር ተወያዩ
አዲስ አበባ፣ ሃምሌ 23፣ 2013 ( ኤፍ ቢ ሲ) የሰላም ሚኒስትር ወይዘሮ ሙፈሪሃት ካሚል ከተባበሩት መንግስታት የፖለቲካና ሰላም ግንባታ ጉዳዮች ዋና ፀሀፊ ዶክተር ሮዝማሪ ዲካርሎ ጋር ተወያዩ፡፡
ሚኒስትሯ በማህበራዊ ትስስር ገፃቸው ባሰፈሩት ፅሁፍ በውይይቱ በኢትዮጵያ ወቅታዊ ጉዳዮች በተለይም በሰሜኑ የሃገሪቱ ክፍል ከአንድ ወገን የተኩስ አቁም ስምምነት በኋላ ስላለው የሰብዓዊ እርዳታ አስመልክቶ በስፋት መክረዋል።
በተጨማሪም ኢትዮጵያ ስለምትገኝበት የለውጥ ሂደት፣ በቅርቡ ስለተካሄደው የምርጫ ሂደት እና በሀገር ዓቀፍ ደረጃ ላለፈው አንድ አመት በመካሄድ ላይ ስላለው ሁሉን አቀፍ የማህበረሰብ የምክክር ሂደትን በተመለከተ ገለጻ ተደርጓል፡፡
ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!