Fana: At a Speed of Life!

ሀገር አቀፍ የወባ ሳምንት እየተካሄደ ነው

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 1፣ 2014(ኤፍ ቢ ሲ)ወባን ማጥፋት ከእኔ ይጀምራል በሚል መሪ ቃል ከጥቅምት 1 እስከ 7 በሀገር አቀፍ ደረጃ የሚከበረዉን የወባ ሳምንት ይፋዊ ማስጀመሪያ መርሀ ግብር በአርባምንጭ ከተማ እየተካሄደ ነው።

በመርሀ ግብሩ ከጤና ሚኒሰቴር ፣ የክልሉ ጤና ቢሮ ሃላፊዎች ፣ የዞንና የወረዳ ባለሙያዎች ተገኝተዋል፡፡

በጤና ሚኒስቴር የበሽታዎች መከላከልናመቆጣጠር ዳይሬክተር ወይዘሮ ሕይወት ሰለሞን በሽታውን ለመከለካል የሁሉም ድርሻ ከፍተኛ መሆኑን ተናግረዋል፡፡

በዘርፉ የሚታየውን ችግር ለመቅረፍም ከባለድርሻ አካለት ጋር ትኩረት ሰጥተን እንሰራለን ብለዋል፡፡

በማቱሳላ ማቴዎስ

ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡

ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.