Fana: At a Speed of Life!

በአማራ ክልል በሰሜን ሸዋ ዞንና በኦሮሞ ብሔረሰብ አስተዳደር ዞን የሚከሰቱ ግጭቶችን ከመሠረቱ ለመፍታት የሚያስችል ውይይት ተካሄደ

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 2፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በአማራ ክልል በሰሜን ሸዋ ዞንና በኦሮሞ ብሔረሰብ አስተዳደር ዞን የሚገኙ የየዞኖቹ የሰላም ኮሚቴ አባላት፣ የሀገር ሽማግሌዎች፣ የሃይማኖት አባቶች እና በየደረጃው የሚገኙ አመራሮች የሚከሰቱ ግጭቶችን ከመሠረቱ ለመፍታት የሚያስችል ውይይት አካሂደዋል።…

የሶማሌ ክልል ልዩ ሀይል በርካታ አውዳሚና ተቀጣጣይ ፈንጂዎችን በቁጥጥር ስር አዋለ

አዲስ አበባ ፣ ነሐሴ 2 ፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የሶማሌ ክልል ልዩ ኃይል አሸባሪው የአልሸባብ ቡድን የሽብር ጥቃት ለመፈፀም በድብቅ ወደ ሀገሪቱ ያስገባቸውን በርካታ አውዳሚና ተቀጣጣይ ፈንጂዎችን በቁጥጥር ስር ማዋሉን ገለፀ። የሶማሌ ክልል ልዩ ኃይል በቁጥጥር ስር ካዋላቸው አደገኛና አውዳሚ…

በኒውክሌር ጣቢያ ላይ የሚደረግ ማንኛውም ጥቃት ራስን የማጥፋት ድርጊት ነው – አንቶኒዮ ጉተሬዝ

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 2፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የኒውክሌር ግጭት ስጋት ከብዙ አሥርት ዓመታት በኋላ ዳግም መመለሱን የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሀፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ ተናገሩ፡፡ ኒውክሌር የታጠቁ ሀገራት መንግስታትም የጦር መሳሪያውን ቀዳሚ ምርጫቸው እንዳያደርጉም ጠይቀዋል።…

127 ነጥብ 6 ሚሊየን ብር የሚያወጡ የኮንትሮባንድ እቃዎች ተያዙ

አዲስ አበባ ፣ ነሐሴ 2 ፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) ባለፉት ስምንት ቀናት 127 ነጥብ 6 ሚሊየን ብር የሚያወጡ የኮንትሮባንድ እቃዎች መያዛቸውን የጉምሩክ ኮሚሽን አስታወቀ፡፡ ኮሚሽኑ ከሐምሌ 21 እስከ 28 ቀን 2014 ዓ.ም ባደረገው ዘመቻ የኮንትሮባንድ እቃዎችን ሲያዘዋውሩ የተገኙ 14 ሰዎችንም…

በአዲስ አበባ ከታሪፍ ጋር በተያያዘ የሚታዩ ችግሮችን ለመፍታት ያለመ ምክክር ተደረገ

አዲስ አበባ ፣ ነሐሴ 1 ፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የህዝብ ትራንስፖርት አገልግሎት እየሰጡ የሚገኙ ተሽከርካሪዎች መንግስት ባወጣው ታሪፍ ብቻ ህብረተሰቡን በሚያገለግሉበት አግባብ ዙሪያ ምክክር ተደርጓል፡፡ ምክክሩ የተደረገው በትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስቴር…

የሐረሪ ክልል በተለያየ ምክንያት ከህዝብ የሚጠብቅባቸውን አገልግሎት መስጠት ባልቻሉ አካላት ላይ ተገቢውን እርምጃ እንደሚወስድ አስታወቀ

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 1፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የሐረሪ ክልል በተለያየ ምክንያት ከህዝብ የሚጠብቅባቸውን አገልግሎት መስጠት ባልቻሉ አካላት ላይ ተገቢውን እርምጃ እንደሚወስድ አስታውቋል፡፡ ክልሉ በመንግስትና በህዝብ መካከል ያለው መሰረታዊ ግንኙነት የአገልጋይና የተገልጋይ ግንኙነት መሆኑን…

ልማት ባንክ በተጠናቀቀው በጀት አመት 11 ቢሊየን ብር የሚጠጋ ገንዘብ ከሰጠው ብድር ሰበሰበ

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 1፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢትዮጵያ ልማት ባንክ በተጠናቀቀው 2014 በጀት አመት 10 ነጥብ 9 ቢሊየን ብር ከሰጠው ብድር መሰብሰብ መቻሉን ገለፀ። ባንኩ የትግራይ ክልል ፕሮጀክቶችን ሳይጨምር የተበላሸ ብድር ደረጃን ወደ 17 በመቶ ማውረድ መቻሉንም አስታውቋል።…

ዳያስፖራው በሀገሪቱ ዘላቂ ጥቅም ላይ ልዩ ትኩረት ሰጥቶ እንዲንቀሳቀስ እየሰራን ነው – የኢትዮጵያ ዳያስፖራ አገልግሎት

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 25፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የዳያስፖራው ማህበረሰብ በሀገሪቱ ዘላቂ ጥቅም ላይ ልዩ ትኩረት ሰጥቶ የበለጠ እንዲንቀሳቀስ ለማድረግ እየሰራ መሆኑን የኢትዮጵያ ዳያስፖራ አገልግሎት አስታወቀ፡፡ ከፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፓሬት ጋር ቆይታ ያደረጉት የአገልግሎቱ ምክትል ዳይሬክተር…

በኢጋድ ቀጣና ሰላምና ልማት ላይ የሚንቀሳቀስ ፎረም በይፋ ሥራ ጀመረ

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 25፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢትዮጵያ የቀድሞ መሪዎች በበላይነት የሚመሩትና በኢትዮጵያና በኢጋድ ቀጣና ሰላምና ልማት ላይ የሚንቀሳቀስ ፎረም በይፋ ሥራ ጀመረ። የአንተርፕረነሪያል ፎረም ፎር ፒስ ኤንድ ዴቨሎፕመንት የተሰኘው መንግሥታዊ ያልሆነ ደርጅት በይፋ ሥራ የማስጀመሪያ…

በንግድ ማጭበርበርና ኮንትሮባንድ ሊታጣ የነበረ ከ50 ቢሊየን ብር በላይ ማዳን መቻሉ ተገለጸ

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 25፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በንግድ ማጭበርበርና በኮንትሮባንድ መንግስት ሊያጣው የነበረን ከ50 ቢሊየን ብር በላይ ማዳን መቻሉን የገቢዎች ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡ የገቢዎች ሚኒስቴርና የጉምሩክ ኮሚሽን ከፍተኛ አመራሮች የተቋሙን የ2014 በጀት ዓመት…