Fana: At a Speed of Life!

ባንኩ ዛሬ በልዩ የውጭ ምንዛሪ ጨረታ አንድ ዶላር በአማካይ 107 ነጥብ 9 ብር ሸጠ

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 1፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ዛሬ ባወጣው ልዩ የውጭ ምንዛሪ ጨረታ አንድ የአሜሪካ ዶላር በአማካይ 107 ነጥብ 9 ብር ዋጋ መሸጡን አስታውቋል፡፡ ባንኩ ዛሬ ነሐሴ 1 ቀን 2016 ዓ.ም የተካሄደውን የልዩ የውጭ ምንዛሪ ጨረታ ውጤት ይፋ አድርጓል።…

ለጎፋ ዞን እስካሁን 210 ነጥብ 5 ሚሊየን ብር በላይ ድጋፍ መደረጉ ተገለጸ

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 1፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጎፋ ዞን በደረሰው የመሬት መንሸራተት አደጋ ጉዳት ለደረሰባቸው ዜጎች እስካሁን ቃል የተገባውን ሳይጨምር 210 ነጥብ 5 ሚሊየን ብር በላይ ድጋፍ መደረጉ ተገልጿል፡፡ ከተደረገው ድጋፍ ውስጥ 92 ነጥብ 5 ሚሊየን ብሩ በጥሬ…

ከ 7 ሺህ በላይ ሕገ- ወጥ ነጋዴዎች ላይ እርምጃ ተወሰደ

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 1፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያውን ተከትሎ ዋጋ በመጨመር እና ምርት በመደበቅ ተግባር ላይ የተገኙ ከ7 ሺህ በላይ ነጋዴዎች እርምጃ እንደተወሰደባቸው የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡ የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ (ዶ/ር)÷…

‘አሰልጣኟ አይደለህም፣ አናውቅህም’ ተብየ ኦሊምፒኩን እንዳልከታተል ተደርጌያለሁ – የአትሌት ጽጌ ዱጉማ አሰልጣኝ

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 1፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) ‘አሰልጣኟ አይደለህም፣ አናውቅህም’ ተብየ ኦሊምፒኩን እንዳልከታተል ተደርጌያለሁ ሲል የአትሌት ጽጌ ዱጉማ አሰልጣኝ ዓለሙ ዋቅጅራ ተናገረ፡፡ አሰልኙ የፓሪስ ኦሊምፒክ መለያ ባጅ መከልከሉን ተክትሎ በኢትይጵያ ኦሊምፒክ ኮሚቴ አመራሮች ላይ ቅሬታውን…

በአፋር ክልል ሕገ-ወጥ ንግድ በፈጸሙ 748 ተቋማት ላይ እርምጃ ተወሰደ

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 1፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የአፋር ክልል ሰሞኑን በንግድ ስርዓቱ ላይ ግብይቱን ባስተጓጓሉ 748 የንግድ ተቋማት ላይ እርምጃ መውሰዱን የክልሉ ንግድና ገበያ ልማት ቢሮ አስታወቀ። የቢሮው ም/ሃላፊ አቶ አደን ሂንከብ እንደገለፁት÷ መንግስት የወሰደውን የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ…

በ5 ሺህ ሜትር የወንዶች ሩጫ ኢትዮጵያውያን አትሌቶች ለፍጻሜ ደረሱ

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 1፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በ33ኛው የፓሪስ ኦሊምፒክ በ5 ሺህ ሜትር የወንዶች ሩጫ አትሌት ሐጎስ ገብረ ሕይወት፣ ቢንያም መሐሪ እና አዲሱ ይሁኔ ለፍጻሜ አልፈዋል፡፡ የ5 ሺህ ሜትር የወንዶች ማጣሪያ ውድድር 6 ሰዓት ከ10 ላይ ተካሂዷል፡፡ በዚህም አትሌት ሐጎስ በምድብ…

ደቡብ ኮሪያ ለኢትየጵያ የ7 ሚሊየን ዶላር ድጋፍ አደረገች

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 1፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የደቡብ ኮሪያ መንግስት በኢትየጵያ ለሰብዓዊ እርዳታ የሚውል የ7 ሚሊየን ዶላር ድጋፍ ማድረጉን አስታውቋል፡፡ ድጋፉ በተባበሩት መንግስታት የልማት ፕሮግራም (ዩኤንዲፒ)፣ በዓለም ምግብ ፕሮግራም (ደብሊዩኤፍፒ)፣ ዓለም አቀፉ የቀይ መስቀል ማሕበር…

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የአዳዲስ ታክስ ሕጎች ትውውቅ መድረክ እየተካሄደ ነው

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 1፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ገቢዎች ቢሮ የበጀት ዓመቱን አፈጻጸምና የ2017 በጀት ዓመት ዕቅድ ዝግጅት እና የታክስ ሕጎች የትውውቅ መድረክ እየተካሄደ ነው፡፡ በመድረኩ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደን ጨምሮ ሌሎች የክልሉ ከፍተኛ የሥራ…

ጎንደር ከተማ ከእስራኤል እህት ከተሞች ጋር ያላትን ግንኙነት ለማጠናከር ያለመ ምክክር ተካሄደ

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 1፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) ጎንደር ከተማ እስራኤል ከሚገኙ እህት ከተሞች ጋር ያላትን ግንኙነት ለማጠናከር ያለመ ምክክር ተካሂዷል፡፡ የጎንደር ከተማ አሥተዳደር ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ ባዩህ አቡሃይ ከእስራኤል ም/አምባሳደር ቶመር ባርላቪ ጋር በቱሪዝምና የእህትማማች ከተሞችን…

በአፋር ክልል የሚንቀሳቀሱ ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች በወቅታዊ ጉዳዮች ላይ ተወያዩ

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 29፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በአፋር ክልል የሚንቀሳቀሱ ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት አባላት በወቅታዊ ሀገራዊ እና ክልላዊ ጉዳዮች ላይ ተወያይተዋል። በመድረኩ የብልጽግና ፓርቲ የአፋር ክልል ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ሃላፊ ሃጂ ኢሴ አደም÷የብልጽግና ፓርቲ ከሌሎች…