Fana: At a Speed of Life!

1 ሺህ 195 ኢትዮጵያውያን ከሳዑዲ ወደ ሀገራቸው ተመለሱ

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 24፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በሳዑዲ ዓረቢያ በችግር ውስጥ የነበሩ 1 ሺህ 195 ኢትዮጵያውያን በዛሬው ዕለት ወደ ሀገራቸው ተመልሰዋል። ተመላሾቹ 1ሺህ 104 ወንዶች፣ 76 ሴቶችና 15 ጨቅላ ህጻናት ሲሆኑ ÷ ከእነዚህ ውስጥም እድሜያቸው ከ18 ዓመት በታች የሆኑ 43 ታዳጊዎች…

በመዲናዋ ወንጀልን ለመከላከል በተደረገ ኦፕሬሽን በርካታ ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ሥር ዋሉ

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 24፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) ወንጀልን ለመከላከልና ወንጀለኞችን ለመቆጣጠር በተደረገ ኦፕሬሽን በርካታ ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ሥር መዋላቸውን የአዲስ አበባ ፖሊስ አስታወቀ። የአዲስ አበባ ፖሊስ ከሰኔ 5 እስከ 19 ቀን 2016 ዓ.ም ለ15 ቀናት በተከናወነ ኦፕሬሽን በርካታ…

በሶማሌ ክልል ለሕፃናት የቤት ለቤት ክትባት መሰጠት ጀመረ

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 24፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በሶማሌ ክልል እድሜያቸው ከ5 ዓመት በታች ለሆኑ ከ450 ሺህ በላይ ሕፃናት የቤት ለቤት ክትባት መሰጠት መጀመሩን የክልሉ ጤና ቢሮ አስታወቀ። ለአንድ ሳምንት የሚቆየውን የክትባት ዘመቻ የክልሉ ጤና ቢሮ ሃላፊ ዶ/ር ሙሴ አህመድ ከዓለም ጤና ድርጅትና…

ም/ጠ/ሚ ተመስገን ጥሩነህ በጋምቤላ የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብር አከናወኑ

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 24፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ በጋምቤላ ክልል የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብር አከናወኑ፡፡ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት ጽሑፍ÷ "የምትተክል ሀገር፣ የሚያጸና ትውልድ" በሚል መሪ ሃሳብ የጀመርነውን…

ፕሮፌሰሮቹ አባት እና ልጅ

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 24፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) ፕሮፌሰር ባዬ ይማም (አባት) እና ፕሮፌሰር ቃለአብ ባዬ ይማም (ልጅ) የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ያፈራቸው ምሁራን ናቸው፡፡ ሁለቱም የከፍተኛ ትምህርት ሕይወታቸውን በአንጋፋው አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ጀምረው በሞያቸው ዩኒቨርሲቲውን እያገለገሉና ተተኪ…

ቦርዱ የቀሪና ድጋሚ ምርጫ ጊዜያዊ ውጤቶችን እያረጋገጠ መሆኑን ገለጸ

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 24፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) ቀሪና ድጋሚ ምርጫ በተካሄደባቸው በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ፣ አፋር፣ ሶማሌ እና ማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልሎች በጊዜያዊነትይፋ የተደረጉ የምርጫ ውጤቶችን እያረጋገጠ መሆኑን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ አስታውቋል፡፡ የቦርዱ የምርጫ ኦፕሬሽን ክፍል ሃላፊ…

በአቶ ሽመልስ አብዲሳ የተመራ ልዑክ በሆሮ ጉዱሩ ወለጋ ዞን የልማት ሥራዎችን እየጎበኘ ነው

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 24፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በኦሮሚያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ሽመልስ አብዲሳ የተመራ የፌዴራል እና የክልሉ ከፍተኛ አመራሮች ልዑክ በሆሮ ጉዱሩ ወለጋ ዞን የልማት ሥራዎችን እየጎበኘ ነው። ርዕሰ መስተዳድር ሽመልስ÷ በዞኑ ከጸጥታ ሥራው ጎን ለጎን እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት…

ከፍተኛ የሥራ ሃላፊዎች የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎችን የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት ጎበኙ

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 24፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የሰላም ሚኒስትር ብናልፍ አንዱአለም እና የትምህርት ሚኒስትር ብርሃኑ ነጋ (ፕ/ር) የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች እየሰጡ ያለውን የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት ተዘዋውረው ጎብኝተዋል፡፡ የዘንድሮው ክረምት የበጎ ፈቃድ አገልግሎት "በጎነትና አብሮነት…

በአውሮፓ ዋንጫ ፈረንሳይ ከቤልጂየም የሚያደርጉት የጥሎ ማለፍ ጨዋታ ይጠበቃል

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 24፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በአውሮፓ ዋንጫ የጥሎ ማለፍ መርሐ ግብር ዛሬ ምሽት ቀጥሎ የሚካሄድ ሲሆን ፈረንሳይና ቤልጂየም የሚያደርጉት ጨዋታ ይጠበቃል፡፡ በ17ኛው የአውሮፓ ዋንጫ የጥሎ ማለፍ መርሐ ግብር ዛሬ ምሽት ሁለት ጨዋታዎች ይደረጋሉ፡፡ በዚህ መሰረትም ምሽት 1…

ኢትዮጵያ ንግድ ባንክና ወልቂጤ ከተማ ድል ቀናቸው

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 23፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክና ወልቂጤ ከተማ ተጋጣሚዎቻቸውን አሸንፈዋል። በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 29ኛ ሳምንት መርሐ ግብር ቀን 9 ሰዓት ላይ ሁለት ጨዋታዎች ተደርገዋል። በዚህ መሰረትም ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ሻሸመኔ ከተማን…