Fana: At a Speed of Life!

የ76 ንጹሃን ዜጎችን ህይወት በአሰቃቂ ሁኔታ እንዲጠፋ ያደረጉ ተከሳሾች እስከ እድሜ ልክ ጽኑ እስራት እንዲቀጡ ተወሰነባቸው

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 12፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል በመተከል ዞን በማንዱራ፣ ዳንጉር እና ፓዊ ወረዳዎች የ76 ንጹሃን ዜጎችን ህይወት በአሰቃቂ ሁኔታ እንዲጠፋ ያደረጉ ተከሳሾች እንደየወንጀል ተሳትፏቸው ከእድሜ ልክ ጀምሮ በጽኑ እስራት እንዲቀጡ ተወሰነ፡፡…

ምንጩ ያልታወቀ 9 ሚሊየን ብር የሚጠጋ ንብረት አካብቷል በተባለ የቀድሞ ፖሊስ አባል ላይ ክስ ተመሰረተ

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 12፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) ከህጋዊ የወር ገቢው ጋር የማይመጣጠንና ምንጩ ያልታወቀ 9 ሚሊየን ብር የሚጠጋ ንብረትና ገንዘብ አካብቶ በተገኘው የፌዴራል ፖሊስ ወንጀል መርማሪ በነበረ ግለሰብ ላይ ክስ ተመሰረተ፡፡ በፌደራል ፖሊስ ወንጀል ምርመራ ቢሮ መርማሪ ሆኖ ሲሰራ…

የፍትህ ሚኒስትሩ እየተከናወነ ባለው የዘርፉ ማሻሻያ ዙሪያ በኢትዮጵያ የአሜሪካ መንግሥት ጉዳይ አስፈጻሚ ጋር ተወያዩ

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 12፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የፍትህ ሚኒስትር ዶክተር ጌዲዮን ጢሞቲዎስ በኢትዮጵያ የአሜሪካ መንግሥት ጉዳይ አስፈጻሚ አምባሳደር ትሬሲ አን ጃኮብሰን ጋር ተወያዩ፡፡ በውይይታቸውም በኢትዮጵያ ለውጡን ተከትሎ በተደረጉ የህግ ማሻሻያዎች እና በሚዲያ ነጻነት ላይ…

5 ሺህ ሄክታር ስፋት ያለው የአባያ ሃይቅ ክፍል በእምቦጭ ተወሯል

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 12፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) አባያ ሀይቅ በእምቦጭ አረም መጠቃቱን የደቡብ ክልል የአከባቢና ደን ባለስልጣን የብዘሃ ህይወት ልማትና ጥበቃ ዳይሬክቶሬት አስታወቀ። የዳይሬክቶሬቱ ኃላፊ አቶ መላኩ ባፋ ፥ እምቦጭ አረም የአባያ ሀይቅን በስፋት እያጠቃ መሆኑን ገልፀው፥…

ዶክተር ሊያ ሰብዓዊ እርዳታን በተመለከተ በኢትዮጵያ የዓለም የምግብ ፕሮግራም ዳይሬክተር ጋር ተወያዩ

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 12፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የጤና ሚኒስትር ዶክተር ሊዩ ታደሰ አዲስ ከተሾሙት በኢትዮጵያ የዓለም የምግብ ፕሮግራም ዳይሬክተር ክላውዴ ጂቢዳር ጋር ተወያይተዋል፡፡   በውይይታቸውም በኢትዮጵያ በግጭት እና በድርቅ ምክንያተ ጉዳት ለደረሰባቸው ዜጎች በሚደረጉ…

ለአምባሳደሮች እና የኤጀንሲ ኃላፊዎች የብሔራዊ ኢኮኖሚ አፈፃፀም ላይ ማብራሪያ ተሰጠ

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 12፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) መንግሥት ለአምባሳደሮች እና ለኤጀንሲ ኃላፊዎች በዘጠኝ ወራት የብሔራዊ ኢኮኖሚ አፈፃፀም ላይ ማብራሪያ ተሰጠ ። በመድረኩ የተሳተፉት የገንዘብ ሚኒስትር አህመድ ሺዴ÷ ባለፉት ሁለት ዓመታት የሀገሪቱ ብሔራዊ ኢኮኖሚ ፈተና የነበሩ…

የጋምቤላ ክልል ያለውን የተፈጥሮ ሐብት መሠረት ላደረገ የአምራች ኢንዱስትሪ ልማት ተዘጋጅቷል- አቶ ኡሞድ ኡጁሉ

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 12፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢትዮጵያ ኢንተርፕራይዝ ከፍተኛ አመራሮች ከጋምቤላ ክልላዊ መንግስት ከፍተኛ ሐላፊዎች ጋር በኢንተርፕራይዞች ልማት ዙርያ ተወያይተዋል፡፡ በውይይቱ በኢትዮጵያ ኢንተርፕራይዝ  ልማት ም/ዋ/ ዳይሬክተር በአቶ ጳውሎስ በርጋ የተመራ ልዑክ ከክልሉ…

በኢትዮጵያ ምርታማነትን ማሳደግ የምርጫ ሳይሆን የህልውና ጉዳይ መሆኑ ተገለፀ

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 12፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በኢትዮጵያ ምርታማነትን ማሳደግ የምርጫ ሳይሆን የህልውና ጉዳይ መሆኑ ተገለፀ። ይህ የተገለጸው "ሀገራዊ አምራችነት " በሚል በጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት የአዲስ ወግ ውይይት በተካሄደበት ወቅት ነው። በውይይቱ…

የአዲስ ከተማ ክ/ከተማ ነዋሪዎች ለተፈናቃዮች 15 ሚሊየን ብር በላይ የሚያወጣ የአይነትድጋፍ አደረጉ

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 12፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ ነዋሪዎች በአሸባሪው ህወሓት ተፈናቅለው ሰሜን ወሎ ዞን በመጠለያ ካፕ ለሚገኙ ወገኖች ከ15 ሚሊየን ብር በላይ የሚገመት የአይነት ድጋፍ አድርገዋል፡፡ በክፍለ ከተማው የቴክኒክ ሙያ ስልጠና…

የተመረጡ ስራዎችን በማከናወን የማህበረሰቡን የኑሮ ጫና ለማቃለል የሚደረገው ጥረት ተጠናክሮ ይቀጥላል-ከንቲባ አዳነች አቤቤ

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 12፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በመዲናዋ የተመረጡ ስራዎችን በመስራት እና ውጤት በማምጣት የማህበረሰቡን የኑሮ ጫና ለማቃለል የሚደረገው ጥረት ተጠናክሮ ይቀጥላል ሲሉ የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ ወይዘሮ አዳነች አቤቤ ገለጹ፡፡   በልደታ ክፍለ ከተማ በቀጣይ 60…