Fana: At a Speed of Life!

እስካሁን ለመከላከያ ሠራዊት 3 ቢሊየን ብር ገቢ ተሰብስቧል

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 26፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) እስካሁን ባለው ሂደት ለመከላከያ ሠራዊቱ 3 ቢሊየን ብር ገቢ መሰብሰቡን የመከላከያ ሚኒስቴር አስታወቀ። የመከላከያ ሚኒስትሩ ዶክተር ቀነዓ ያደታ ለሰራዊቱ የተደረገውን የሃብት ማሰባሰብ አስመልክቶ መግለጫ ሰጥተዋል፡፡…

የሶማሌ ክልል ልዩ ሃይል እና ፖሊስ አባላት ለመከላከያ ሰራዊት ደም ለገሱ

አዲስ አበባ ፣ ነሐሴ 26፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ ) የሶማሌ ክልል ልዩ ሃይል እና ፖሊስ አባላት ለሀገር መከላከያ ሰራዊት እና ለልዩ ሃይል አባላት ደም ለግሰዋል፡፡   የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር ሙሐመድ አሊ÷የሀገር አንድነትን ለማረጋገጥ በግንባር ለተሰለፉ የጸጥታ ሃይሎች…

አዲሱ ፍኖተ ካርታ አጠቃላይ የትምህርት ዘርፉን ክፍተቶች ታሳቢ ያደረገ ነው-ትምህርት ሚኒስቴር

አዲስ አበባ ፣ ነሐሴ 26፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) አዲሱ ፍኖተ ካርታ አጠቃላይ የትምህርት ዘርፉን ክፍተቶች ታሳቢ ያደረገ መሆኑን የትምህርት ሚኒስትሩ ዶክተር ኢንጂነር ጌታሁን መኩሪያ ገለጹ፡፡ አዲሱ ፍኖተ ካርታ ከዚህ ቀደም በነበረው ስርዓት ትምህርት ላይ የነበሩ ክፍተቶችን የሚሞላ እና በጥናት…

የተጣለብንን ህዝባዊ አደራ ለመወጣት ህይወታችን እስከመስጠት ቁርጠኞች ነን-የአፋር ክልል ም/ቤት አባላት

አዲስ አበባ ፣ ነሐሴ 26፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) የተጣለብንን ህዝባዊና ሀገራዊ አደራ በብቃት ለመወጣት ደም ከመለገስ ጀምሮ ህይወታችንን እስከመስጠት ድረስ ቁርጠኞች ነን ሲሉ የአፋር ክልል ምክር ቤት አባላት ገለጹ።   የምክር ቤቱ አባላት  ለሀገር መከላከያ ሠራዊትና ለሌሎች ጸጥታ…

በሶማሌ፣ ሐረሪ እና ደቡብ ክልሎች ለሚካሄደው ምርጫ የመራጮች ምዝገባ ተጀመረ

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 26፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) በሶማሌ፣ ሐረሪ እና ደቡብ ክልሎች መስከረም 20 ቀን 2014 ዓ.ም ለሚካሄደው ድምጽ አሰጣጥ የመራጮች ምዝገባ መጀመሩን የኢትዮጵያ ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ አስታውቋል፡፡ በመራጮች ምዝገባ ሂደት ላይ በታዩ ጉልህ ግድፈቶች፣ በመራጮች ምዝገባ…

ብሪታኒያ በአፍጋን የቀሩ ዜጎችን ለማስወጣት ከታሊባን ጋር እየመከረች ነው

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 26፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) ብሪታኒያ በአፍኒስታን የቀሩ የሀገሯን እና ሌሎች ዜጎችን ማስወጣት በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ከታሊባን ጋር በኳታር ዶሃ እየመከረች ነው፡፡   ውይይቱ ታሊባን አፍጋኒስታንን ለቀው ለሚወጡ ዜጎች ያስቀመጠውን ቀነ ገደብ ማራዘሙን ተከትሎ…

ደረጃውን የጠበቀ የበግ ቆዳ በማምረት ውጤት ላስመዘገቡ ፋብሪካዎች እውቅና ተሰጠ

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 26፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) ከፍተኛ ጥራት ያለው የኢትዮጵያ የበግ ቆዳ በማምረት ውጤት ላስመዘገቡ አራት ፋብሪካዎች ዕውቅና ተሰጣቸው፡፡   በዘርፉ ዕውቅና ያገኙ ፋብሪካዎችም ባህርዳር፣ ኒው ዊንግ ፣ ፒታርድ እና ኤሊኮ የተሰኙ የቆዳ ፋብሪካዎች መሆናቸውን…

በጎንደር ከአሸባሪው ህወሓት ጋር ግንኙነት ያላቸው 78 ሰዎች በቁጥጥር ስር ዋሉ

አዲስ አበባ ፣ ነሐሴ 25 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) በጎንደር ከተማ ከአሸባሪው የህውሓት ቡድን ጋር ቀጥተኛ ግንኙነት ያላቸው 78 ሰዎች በቁጥጥር ስር ውለው ምርመራ እየተደረገባቸው መሆኑ ተገለጸ፡፡ የከተማ አስተዳደሩ ፓሊስ መምሪያ ሃላፊ ኮማንደር አየልኝ ታክሎ ለፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት…

ጠ/ሚ ዐቢይ ከጂቡቲው ፕሬዚዳንት ኢስማኤል ዑመር ጊሌ ጋር ተወያዩ

አዲስ አበባ ፣ ነሐሴ 25 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ከጂቡቲው ፕሬዚዳንት ኢስማኤል ዑመር ጊሌ ጋር በሁለትዮሽ ጉዳዮች ዙሪያ በስልክ ተወያዩ። በውይይታቸውም የሁለቱን ሃገራት ታሪካዊ ግንኙነት በሚያጠናክሩ ጉዳዮች ዙሪያ መምከራቸውን ኢዜአ…

ዩኒሴፍ ለተፈናቃዮች ከ30 ሚሊየን ብር በላይ የሚያወጣ ድጋፍ አደረገ

አዲስ አበባ ፣ ነሐሴ 25 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) የተመድ ህጻናት መርጃ ድርጅት (ዩኒሴፍ) በአሸባሪው ህወሓት ወረራ ምክንያት ችግር ለደረሰባቸው እና ለተፈናቀሉ ዜጎች ከ30 ሚሊየን ብር በላይ የሚያወጡ የተለያዩ ቁሳቁሶችን አበረከተ።   ድጋፉን የተረከቡት የአማራ ክልል…