Fana: At a Speed of Life!

የሩሲያው ፕሬዚዳንት የቻይናን ሚዛናዊ አቋም አወደሱ

አዲስ አበባ፣ መስከረም 5፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) ፕሬዚዳንት ፑቲን ቻይና በዩክሬኑ ጦርነት ላይ እያራመደች ያለውን ሚዛናዊና ገለልተኛ አቋም አድንቀው አሜሪካ በታይዋን ላይ እያሳየች ያለችውን ኢፍትሃዊ አካሄድ ኮነኑ፡፡ የሩስያው ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን ከቻይናው አቻቸው ፕሬዚዳንት ሺ ጂንፒንግ…

መድሃኒት የተላመደ የቲቢ በሽታን ለመቆጣጠር ውጤታማ ስራ ተሰርቷል – ጤና ሚኒስቴር

አዲስ አበባ፣ መስከረም 5፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) መድሃኒት የተላመደ የቲቢ በሽታን ለመቆጣጠር የተሰሩ ተግባራት ውጤት ማስገኘታቸውን የጤና ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡ የጤና ሚኒስቴር የበሽታዎች መከላከል ዳይሬክቶሬት ዓመታዊ የቲቢና የሥጋ ደዌ መርሐ ግብር የሥራ አፈጻጸም ግምገማ ተካሂዷል፡፡…

አምባሳደር ሌንጮ የሳዑዲ ዓረቢያ ባለሀብቶች በኢንቨስትመንት ዘርፎች እንዲሳተፉ ጥሪ አቀረቡ

አዲስ አበባ፣ መስከረም 5፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በሳዑዲ ዓረቢያ የኢትዮጵያ አምባሳደር ሌንጮ ባቲ የሳዑዲ ዓረቢያ ባለሀብቶች መዋዕለ ንዋያቸውን በኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ላይ እንዲያውሉ ጥሪ አቀረቡ። አምባሳደር ሌንጮ ከቪአይኤ መርከብ ድርጅት ማኔጂንግ ዳይሬክተርና ምክትል ሊቀመንበር ቱርኪ…

የሐረሪ ክልል በወቅታዊ ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ ከከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ምሁራን ጋር መከረ

አዲስ አበባ፣ መስከረም 5፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የብልጽግና ፓርቲ የሐረሪ ክልል ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት በክልሉ ከሚገኙ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ምሁራን ጋር በወቅታዊ ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ ተወያየ፡፡ የጽህፈት ቤቱ ኃላፊ አቶ አብዱጀባር መሀመድ ፥ ህዝቡ የሀገርን ክብርና የዜጎችን ደህንነት…

የጅማ ዞን ለመከላከያ ሠራዊት ከ30 ሚሊየን ብር በላይ ድጋፍ አደረገ

አዲስ አበባ፣ መስከረም 5፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የጅማ ዞን ነዋሪዎች ለሀገር መከላከያ ሠራዊት ከ30 ሚሊየን ብር በላይ ድጋፍ አድርገዋል፡፡ የጅማ ዞን ነዋሪዎች ከዚህ ቀደምም ለሠራዊቱ ተመሳሳይ ድጋፍ ያደረጉ ሲሆን ፥ የዛሬው ሁለተኛ ዙር መሆኑ ተመላክቷል። የዞኑ ነዋሪዎች የሀገር…

በቡና የወጪ ንግድ ስኬት አስተዋጽዖ ላበረከቱ አካላት የዕውቅና ሥነ ስርዓት ተካሄደ

አዲስ አበባ፣ መስከረም 5፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በተጠናቀቀው በጀት ዓመት በቡና የወጪ ንግድ በተመዘገበው ስኬት አስተዋጽዖ ላበረከቱ አካላት የዕውቅና ሥነ ስርዓት ተካሄደ፡፡ ‘’ቡናችን ለአብሮነታች እና ለብልፅግናችን’’ በሚል ርዕስ የኢትዮጵያ ቡና ቀን እየተከበረ ይገኛል፡፡ በመርሐ ግብሩ…

የዓለም ጤና ድርጅት የኮቪድ-19 ወረርሽኝ ሊያገረሽ እንደሚችል አስጠነቀቀ

አዲስ አበባ፣ መስከረም 5፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የዓለም ጤና ድርጅት በኮቪድ-19 ስርጭት የሚሞቱት ሰዎች ቁጥር እየቀነሰ ቢመጣም ዳግም ሊያገረሽ እንደሚችል አስጠነቀቀ። ድርጅቱ ወደፊት የኮሮና ቫይረስ ሊያገረሽ እንደሚችል በመጥቀስ፥ ሀገራት ሊፈጠሩ ለሚችሉ ሁኔታዎች ሁሉ ነቅተው በመጠበቅ…

ባህር ዳር ከተማ ደግአረገ ይግዛውን በአሰልጣኝነት ሾመ

አዲስ አበባ፣ መስከረም 5፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) ደግአረገ ይግዛው የባህር ዳር ከተማ እግር ኳስ ክለብ አሰልጣኝ በመሆን ተሾሙ፡፡ የቀድሞው የክለብ አሰልጣኝ ኢንስትራክተር አብርሃም መብራቱ የፊፋ የቴክኒክ ባለሙያ ሆነው መመረጣቸው ይታወሳል። ይህን ተከትሎም አሠልጣኙ ቀሪ የአንድ ዓመት ውል…

ኤጀንሲው የመዲናዋን የትራፊክ ፍሰት የሚያሻሽሉ ስራዎችን እየሰራሁ ነው አለ

አዲስ አበባ፣ መስከረም 5፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የትራፊክ ማኔጅመንት ኤጀንሲ የትራፊክ ፍሰት የሚያሻሽሉ ስራዎችን እየሰራሁ ነው ሲል አስታወቀ፡፡ ወቅቱ ትምህርት ቤቶች ተማሪዎቻቸውን ተቀብለው የሚያስተምሩበት ወቅት ከመሆኑ ጋር በተያያዘ ኤጀንሲው ተለዋዋጭ…

የመዲናዋ አስተዳደር በመሬት ወረራና በፀጥታ ጉዳዮች ላይ በትኩረት መሥራ አለበት ተባለ

አዲስ አበባ፣ መስከረም 4፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ)የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በመሬት ወረራና በፀጥታ ጉዳዮች ላይ በትኩረት መሥራት እንዳለበት የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት ተናገሩ፡፡ ከአዲስ አበባ የተመረጡ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት ከአስተዳደሩ ከፍተኛ አመራሮች ጋር በመዲናዋ…