Fana: At a Speed of Life!

ሩሲያ በአውሮፓ ህብረት አመራሮች ላይ የጉዞ እገዳ ጣለች

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 23፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የአውሮፓ ህብረት አመራሮች ወደ ሩሲያ እንዳይገቡ መታገዳቸውን የሩሲያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ገለጸ፡፡ በአመራሮቹ ላይ የተጣለው እገዳ ሞስኮ ዩክሬን ላይ ከወሰደችው ወታደራዊ እርምጃ ጋር በተያያዘ በምዕራባውያን ለተጣለባት ማዕቀብ የአጸፋ ምላሽ…

በሳዑዲ አረቢያ እስር ቤቶችና ማዕከላት በአስቸጋሪ ሁኔታ የነበሩ 2 ሺህ 111 ዜጎች ወደ ሀገራቸው ተመልሰዋል

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 23፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) ካለፈው ረቡዕ ጀምሮ በሳዑዲ አረቢያ እስር ቤቶች እና ማዕከላት በአስቸጋሪ ሁኔታ ላይ የነበሩ 2 ሺህ 111 ዜጎች ወደ ሀገራቸው መመለሳቸውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ዴኤታ አምባሳደር ብርቱካን አያኖ ገለጹ፡፡ በዛሬው ዕለት ብቻ ከ1 ሺህ 420…

የመድሃኒትና ህክምና ቁሳቁስ እጥረት ህሙማንን ለመርዳት ፈታኝ ሁኔታ ፈጥሯል – የጥቁር አንበሳ ሆስፒታል ባለሙያዎች

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 22፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የመድሃኒትና ህክምና ቁሳቁስ እጥረት ህሙማንን ለመርዳት ፈታኝ ሁኔታ መፍጠሩን የጥቁር አንበሳ ሆስፒታል የህክምና ባለሙያዎች ተናገሩ፡፡ የተለያዩ የጥቁር አንበሳ ህክምና ባለሙያዎች ከፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት ባደረጉት ቆይታ፥ ከግብዓት አቅርቦት…

የጤና ሚኒስቴር እና የክልል ጤና ቢሮዎች በዘርፉ ቀጣይ አቅጣጫዎች ላይ ለመግባባት የሚያስችል የጋራ መድረክ ማካሄድ ጀመሩ

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 22፣2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የጤና ሚኒስቴር፣ የክልል የጤና ቢሮዎች እና የተጠሪ ተቋማት ከፍተኛ አመራሮች በዘርፉ ቀጣይ አቅጣጫዎች ላይ ለመግባባት የሚያስችል የጋራ መድረክ ማካሄድ ጀመሩ። የጤና ሚኒስትር ዴኤታ ዶክተር ደረጀ ዱጉማ÷ የጤናው ዘርፍ ከፍተኛ አመራሮች የጋራ…

አሜሪካ የኢኮኖሚ እና ንግድ ጉዳዮችን ለፖለቲካ ፍጆታ ከማዋል እንድትቆጠብ ቻይና ጠየቀች

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 22፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) አሜሪካ በቻይና የኢኮኖሚ እና ንግድ ጉዳዮች ላይ ያላትን የተሳሳተ አቀራረብ በአስቸኳይ እንድታርም የቻይና ንግድ ሚኒስቴር አስጠነቀቀ፡፡ የቻይና ንግድ ሚኒስቴር ÷ ቻይና በምታደርጋቸው የንግድ እንቅሥቃሴዎች ላይ ጫና በመፍጠር ኢኮኖሚዋን ለመጉዳት…

በድርቅ ለተጎዱ ዜጎች የሚውል የ45 ሚሊየን ብር የምግብ ፍጆታ ድጋፍ ተደረገ

አዲስ አበባ ፣ መጋቢት 22 ፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) አዋሽ ባንክ በኦሮሚያ ክልል በድርቅ ለተጎዱ ዜጎች የሚውል የ45 ሚሊየን ብር ግምት ያለው የምግብ ፍጆታ ድጋፍ አደረገ፡፡ ድጋፋ ድርቅ በተከሰተባቸው ቦረና፣ ጉጂና ባሌ አካባቢዎች ለሚገኙ ዜጎች ተደራሽ ይሆናል ተብሏል። የአዋሽ ባንክ…

ታላቁ የረመዳን ወር ይቅር የምንባባልበት ነው – ተቀዳሚ ሙፍቲ ሐጅ ዑመር ኢድሪስ

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 22፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) ታላቁ የረመዳን ወር ይቅር የምንባባልበት መሆኑን የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ፕሬዚዳንት ተቀዳሚ ሙፍቲ ሐጅ ዑመር ኢድሪስ ገለጹ፡፡ ተቀዳሚ ሙፍቲ ሐጅ ዑመር ኢድሪስ የታላቁ ረመዳንን ወር ፆም አስመልክቶ መግለጫ ሰጥተዋል ።…

ሩሲያ እና ዩክሬን የሰላም ድርድራቸውን ነገ በኦንላይን ሊቀጥሉ ነው

አዲስ አበባ ፣ መጋቢት 22 ፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) ሩሲያ እና ዩክሬን የሰላም ድርድራቸውን ነገ በቀጥታ (ኦንላይን) ሊቀጥሉ ነው። የዩክሬን ተደራዳሪ ዴቪድ አራካሚያ ሁለቱ ሃገራት በቱርክ ስኬታማ ውይይት ማድረጋቸውን አስታውሰው፥ በነገው እለት በኦንላይን ቀጣይ ድርድራቸውን ያካሂዳሉ ብለዋል።…

ከነገ ጀምሮ ለነባር እና ለአዳዲስ የሃይማኖት ቴሌቪዥን አመልካቾች ፈቃድ መስጠት ሊጀመር ነው

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 22፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) ከመጋቢት 23 2014 ዓ.ም ጀምሮ ለነባር እና ለአዳዲስ የሃይማኖት ቴሌቪዥን አመልካቾች ፈቃድ መስጠት እንደሚጀምር የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙሃን ባለስልጣን ገለጸ። ባለስልጣኑ በሃይማኖት ብሮድካስት ረቂቅ መመሪያ ዙሪያ ውይይት እያደረገ ነው።…

የሶማሌ ክልል ህዝብን ህይወት ለማሻሻል ለሚደረገው ጥረት ድጋፍ እንደሚያደርጉ ለጋሽ ድርጅቶች ገለጹ

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 20፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የሶማሌ ክልል ህዝብን ህይወት ለማሻሻል የክልሉ መንግስት የሚያደርገውን ጥረት እንደሚደግፉ ዓለምአቀፍ የግብረ ሰናይ ድርጅቶች አመራሮች ገለጹ፡፡ የሶማሌ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ሙስጠፌ መሀመድ እና የክልሉ ከፍተኛ አመራር አካላት ከዓለም አቀፍ…