Fana: At a Speed of Life!

የአፍሪካ አህጉራዊ ነጻ ንግድ ቀጣና ሴክሬታሪያት ዋና ጸሐፊ አዲስ አበባ ገቡ

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 23፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የአፍሪካ አህጉራዊ ነጻ ንግድ ቀጣና ሴክሬታሪያት ዋና ጸሐፊ ዋምኬሌ ሜኔ ለይፋዊ የሥራ ጉብኝት አዲስ አበባ ገብተዋል፡፡ ለዋና ጸሃፊው የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ዴዔታ ያስሚን ወሐብረቢ በቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ አቀባበል…

በስልጤ ዞን ለጎርፍ አደጋ ዘላቂ መፍትሄ ለመስጠት እየተሰራ መሆኑ ተጠቆመ

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 23፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በስልጤ ዞን በተደጋጋሚ ለሚከሰተው የጎርፍ አደጋ ዘላቂ መፍትሄ ለመስጠት እየሰራ መሆኑን የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን አስታወቀ። የክልሉ አደጋ ስጋት ኮሚሽነር ማዕረጉ ማቴዎስ ለፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት እንደገለጹት…

በዘንድሮው የመኸር ወቅት 10 ሚሊየን ሄክታር መሬት በክላስተር ለምቷል – የግብርና ሚኒስቴር

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 22፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በዘንድሮው የመኸር ወቅት 10 ሚሊየን ሄክታር መሬት በክላስተር መልማቱን የግብርና ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡ ከፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት ጋር ቆይታ ያደረጉት በግብርና ሚኒስቴር የሰብል ልማት መሪ ስራ አስፈጻሚ ኢሳያስ ለማ፥ በ2016/17 የመኸር…

ኢራን ከአሜሪካ ጋር በኒውክሌር ዙሪያ ለመደራደር በሯን ከፈተች

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 22፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) ኢራን ከአሜሪካ ጋር በኒውክሌር ዙሪያ ለመደራደር ዝግጁ መሆኗን አስታውቃለች፡፡ የኢራን ከፍተኛ መሪ አያቶላህ አሊ ካሜኒ በቴህራን የኒውክሌር ፕሮግራም ላይ ከአሜሪካ ጋር እንደገና ለመደራደር ለሀገሪቱ መንግስት "ምንም እንቅፋት የለም" ብለዋል።…

10 ሺህ የዝንጀሮ ፈንጣጣ መከላከያ ክትባት ናይጄሪያ ደረሰ

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 22፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) 10 ሺህ የዝንጀሮ ፈንጣጣ መከላከያ ክትባት ናይጄሪያ ደረሰ። የዝንጀሮ ፈንጣጣ በሽታ የዓለም የጤና ስጋት መሆኑ ከተገለጸ ወዲህ ክትባቱን በመረከብ ናይጄሪያ የመጀመሪያዋ አፍሪካዊት ሀገር መሆኗ ተገልጿል። በዓለም የጤና ድርጅት የዓለም የጤና…

ገቢሳ ኤጀታ (ፕ/ር) የዓመቱ የሰብል ልማት ተመራማሪ ተብለው ተመረጡ

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 22፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የአሜሪካው ስመጥር ፑርዱ ዩኒቨርሲቲ ትውልደ ኢትዮጵያዊው ገቢሳ ኤጀታን (ፕ/ር) በአከናወኑት የግብርና ምርምር ሥራ የዓመቱ የሰብል ልማት ተመራማሪ አድርጎ መርጧል፡፡ ገቢሳ ኤጀታ (ፕ/ር) በተለያየ ጊዜ በአካሄዱት ምርምር “ሃይብሪድ” የሆኑ የማሽላ…

ክልሉ የበቆሎ ምርጥ ዘር ፍላጎቱን በራሱ አቅም ለመሸፈን እየሠራ መሆኑን አስታወቀ

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 22፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በዚህ ዓመት የበቆሎ ምርጥ ዘር ፍላጎቱን ከ50 በመቶ በላይ በራሱ አቅም ለመሸፈን እየሠራ መሆኑን የሲዳማ ክልል እርሻና ተፈጥሮ ሀብት ልማት ቢሮ አስታወቀ፡፡ ላለፉት ዓመታት የሚያስፈልገው ምርጥ ዘር ከ70 በመቶ በላይ የሚሸፈነው በሌሎች ክልሎች…

አሜሪካ ከፌስቡክ ላይ የኮቪድ-19 የተወሰኑ ይዘቶች እንዲነሱ ግፊት አድርጋ ነበር ተባለ

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 21፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የፕሬዚዳንት ጆ ባይደን አሥተዳደር በ2021 የኮቪድ-19 የተወሰኑ ይዘቶች ከፌስቡክ እንዲወገዱ ለወራት በተደጋጋሚ ግፊት ማድረጉን የሜታ ኩባንያ መስራች ማርክ ዙከር በርግ አመላከቱ፡፡ ዙከር በርግ ለሀገሪቱ ምክር ቤት የፍትሕ ኮሚቴ በጻፉት ደብዳቤ÷…

የግድቡ ተጨማሪ ተርባይኖች ወደ ሥራ መግባት ኢትዮጵያ ቀጣናውን በኤሌክትሪክ ኃይል ለማስተሳሰር የምታደርገው ጥረት አመላካች ነው ተባለ

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 21፣ 2016(ኤፍ ቢ ሲ) የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ተጨማሪ ሁለት ተርባይኖች ወደ ሥራ መግባት ኢትዮጵያ ቀጣናውን በኤሌክትሪክ ኃይል ለማስተሳሰር የምታደርገው ጥረት አመላካች ነው ሲሉ የቀድሞ የግድቡ ተደራዳሪና የውኃ ኃብት ተመራማሪው ፈቅ አሕመድ ነጋሽ ገለጹ።…

50 ሚሊየን ሊትር የምግብ ዘይት ወደሀገር ውስጥ እየተጓጓዘ ነው

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 20፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) 50 ሚሊየን ሊትር የምግብ ዘይት ከጅቡቲ ወደ ኢትዮጵያ እየተጓጓዘ መሆኑ ተገለጸ፡፡ ከጅቡቲ ወደ ተለያዩ የኢትዮጵያ ክፍሎች እየተጓጓዘ ያለው የምግብ ዘይት የኑሮ ውድነትን ለማሻሻል እና ለመጪው የዘመን መለወጫ በዓል የገበያ ዋጋን ለማረጋጋት ታስቦ…