Fana: At a Speed of Life!

ከ343 ሚሊየን ብር በላይ ግምታዊ ዋጋ ያላቸው የኮንትሮባንድ እቃዎች ተያዙ

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 26፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) ከ343 ሚሊየን ብር በላይ ግምታዊ ዋጋ ያላቸው የኮንትሮባንድ እቃዎች መያዙን የጉምሩክ ኮሚሽን አስታወቀ፡፡ ኮሚሽኑ ከጥቅምት 16 እስከ 22 ቀን 2016 ዓ.ም  በተለያዩ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤቶች ባደረገው ክትትል ነው እቃዎቹ የተያዙት፡፡…

ችግኝ መትከል ብቻ ሳይሆን ጸድቆ በራሱ እስኪቆም  መንከባከብ አስፈላጊ ነው – አቶ ሽመልስ  አብዲሳ

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 26፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) ችግኝ መትከል ብቻ ሳይሆን ጸድቆ በራሱ እስኪቆም ድረስ በዘላቂነት መንከባከብ አስፈላጊ ነው ሲሉ የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ሽመልስ አብዲሳ ገለጹ፡፡ ርዕሰ መስተዳድሩ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት ጽሑፍ÷የአካባቢ ጥበቃ ከክልሉ ዘጠኝ…

የኢትዮጵያና ሕንድን የንግድ  ግንኙነት ማጠናከር ያለመ ውይይት ተካሄደ

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 26፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢትዮጵያ እና ሕንድን የንግድ ግንኙነት ማጠናከርና በመካከላቸው ያለውን የንግድ ሚዛን ማስተካከል የሚያስችል ውይይት ተካሂዷል፡፡ በውይይቱ የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ገብረመስቀል ጫላ ÷ኢትዮጵያ እና ሕንድ ረጅም ጊዜያትን ያስቆጠረ የንግድ…

የግብርና ኮሜርሻላይዜሽን ክላስተር ፕሮግራም ኢኮኖሚን ለማሳደግ ሚናው ከፍተኛ መሆኑ ተገለጸ

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 26፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የግብርና ኮሜርሻላይዜሽን ክላስተር ፕሮግራም ምጣኔ ሃብትን ለማሳደግ ያለው አስተዋጽኦ ከፍተኛ መሆኑን የግብርና ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡ የግብርና ኮሜርሻላይዜሽን ክላስተር ፕሮግራም የ2015 በጀት ዓመት የዕቅድ አፈፃፀም እና የ2016 በጀት ዓመት…

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ነጻ የሕግ ድጋፍ አገልግሎት ስትራቴጂ ወደ ስራ መግባቱ ተመላከተ

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 26፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢትዮጵያ “ብሔራዊ ነጻ የሕግ ድጋፍ አገልግሎት ስትራቴጂ” ፀድቆ ወደ ሥራ መግባቱን የፍትህ ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡ የፍትህ ሚኒስትር ዴኤታ አለምአንተ አግደው÷ ስትራተጂው የሕግ ድጋፍ ለማግኘት የገንዘብ አቅም የሌላቸዉ ዜጎች የመዳኘት መብት…

አሜሪካ በጋዛ ተኩስ አቁም እንዲደረስ የማትፈቅድ ከሆነ ዋጋ ትከፍላለች – ኢራን

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 26፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) አሜሪካ በጋዛ ተኩስ አቁም እንዲደረስ የማትፈቅድ ከሆነ ዋጋ ትከፍላለች ስትል ኢራን አስጠነቀቀች፡፡ ቴህራን ዋሺንግተን በመካከለኛው ምስራቅ ያለው ግጭት እንዲባባስ እያደረገች ነው ስትል ከሳለች። የኢራኑ መካለከያ ሚኒስትር ሞሃመድ ሬዛ…

በክልሉ እየተከናወኑ የሚገኙ ሰው ተኮር ሥራዎች ተጠናክረው ይቀጥላሉ – አቶ ኦርዲን በድሪ

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 24፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በክልሉ የሕዝብን ችግር ለመቅረፍ እየተከናወኑ የሚገኙ ሥራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የሐረሪ ክልል ርዕሰ መሥተዳድር ኦርዲን በድሪ ገለጹ፡፡ የሐረሪ ክልል መስተዳድር ምክር ቤት ሲያካሂደው የቆየው የ2016 የመጀመሪያ ሩብ ዓመት ዕቅድ አፈጻጸም…

የኢትዮጵያ እና የኮሪያ ሪፐብሊክ ፓርላማዎች ግንኙነታቸውን  ለማጠናከር እንደሚሰሩ አስታወቁ

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 22፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢትዮጵያ እና የደቡብ ኮሪያ ሪፐብሊክ ፓርላማዎች ግንኙነታቸውን  የበለጠ ለማጠናከር እንደሚሰሩ ገለፁ፡፡ በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ከውጭ ግንኙነትና የሰላም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ዲማ ነገዎ (ዶ/ር) ከደቡብ ኮሪያ የፓርላማ ልዑክ  ጋር…

የአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ጉባኤን ለማስተናገድ ቅድመ ዝግጅት እየተደረገ መሆኑ ተገለፀ

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 22፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) 37ኛውን የአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ጉባኤን እና 44ኛውን የአስፈጻሚ ምክርቤት ስብሰባ ለማስተናገድ ቅድመ ዝግጅት እተደረገ መሆኑን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ብርቱካን አያኖ ገለፁ፡፡ በመጭው የካቲት ወር በአዲስ አበባ የሚካሄደውን…

በፕሪሚየር ሊጉ ሀዋሳ ከተማና ቅዱስ ጊዮርጊስ ድል ቀንቷቸዋል

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 22፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በ5ኛ ሳምንት የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ሀዋሳ ከተማ እና ቅዱስ ጊዮርጊስ ተጋጣሚዎቻቸውን አሸንፈዋል፡፡ ቀን 9 ሰዓት ላይ ሲዳማ ቡናን የገጠመው ሀዋሳ ከተማ በእዮብ አለማየሁ ብቸኛ ግብ 1 ለ 0 በማሸነፍ ወሳኝ ሶስት ነጥብ አሳክቷል፡፡…