Fana: At a Speed of Life!

አበረታች ሂደቶች የታዩበት የአሜሪካ እና ኢራን ድርድር …

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 15፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ፓኪስታን አሜሪካ እና ኢራንን ለመጨረሻ ጊዜ ለማሸማገል በቀረበው የድርድር ሀሳብ በሁለቱ ወገኖች በኩል ተስፋ ሰጭ ሂደቶች እየታዩ ነው አለች፡፡ ፓኪስታን ይህን ያለችው የሀገሪቱ ጦር አዛዥ ፊልድ ማርሻል አሲም ሙኒር አሜሪካ እና ኢራንን…

ኢትዮጵያን ከፍ ለማድረግ የሚተጉ ወጣቶችን መመልከት በበለጠ ትጋት እንድንሰራ መነሳሳትን ይፈጥርልናል – ከንቲባ አዳነች አቤቤ

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 15፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ ኢትዮጵያን ከፍ ለማድረግ የሚተጉ ወጣቶችን መመልከት በበለጠ ትጋት እንድንሰራ ትልቅ መነሳሳትን ይፈጥርልናል አሉ። ከንቲባዋ ‘ትውልዱ ገብቶታል’ በሚል መሪ ሀሳብ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው…

በ24 ሰዓት ውስጥ 25 መርከቦች በሆርሙዝ ሰርጥ አልፈዋል – ኢራን 

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 15፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የኢራን አብዮታዊ ዘብ ባለፉት 24 ሰዓት ውስጥ 25 የንግድ መርከቦች በሆርሙዝ ሰርጥ አልፈዋል አለ፡፡ የአብዮታዊ ዘቡ የባህር ኃይል እንዳስታወቀው÷ ኢራን ያስቀመጠችውን የቁጥጥር እና የደህንነት መስፈርቶችን በማሟላት በሆርሙዝ ሰርጥ የንግድ…

በርትተን ከሰራን ሀገራችን ለአፍሪካ ተምሳሌት ትሆናለች – ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር)

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 15፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በርትተን ከሰራን እና ከተጋገዝን ሀገራችን ለአፍሪካ ተምሳሌት ትሆናለች አሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ የግራንዴር ሴራሚክ ፋብሪካን መርቀው አገልግሎት ባስጀመሩበት ወቅት ባስተላለፉት መልዕክት፤ በርትተን ከሰራን…

ኒኮ ኦራይሊ የፕሪሚየር ሊጉ ምርጥ ወጣት ተጫዋች ሽልማትን አሸነፈ

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 15፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) እንግሊዛዊው የማንቼስተር ሲቲ ተጫዋች ኒኮ ኦራይሊ የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ምርጥ ወጣት ተጫዋች ሽልማትን አሸንፏል፡፡ ከክለቡ አካዳሚ የተገኘው የ21 ዓመቱ ተጫዋች ከደጋፊዎች በተሰበሰበ ድምፅ ነው የምርጥ ወጣት ተጫዋች ሽልማትን ማሸነፍ…

በወታደራዊ ሥነ ምግባር የታነጸ ገለልተኛ ሠራዊት እየተገነባ ነው – ኮሚሽነር ጀነራል ደመላሽ ገ/ሚካኤል

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 15፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የፌደራል ፖሊስ ጠቅላይ አዛዥ ኮሚሽነር ጀነራል ደመላሽ ገ/ሚካኤል በአስተሳሰብና አደረጃጀት ገለልተኛ የሆነ ሠራዊት እየተገነባ ነው አሉ። የኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ በተለያዩ የትምህርት መስኮች ያሰለጠናቸውን ዕጩ መኮንኖች በዛሬው ዕለት…

የኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ የጸረ ሠላም ኃይሎችን ድርጊት የማክሸፍ አቅም ገንብቷል – ፕሬዚዳንት ታዬ

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 15፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀ ሥላሴ የኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ ከውስጥም ሆነ ከውጭ የሚነሱ የጸረ ሠላም ኃይሎችን ድርጊት የማክሸፍ አቅም ገንብቷል አሉ። የኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ በተለያዩ የትምህርት መስኮች ያሰለጠናቸውን ዕጩ መኮንኖች በዛሬው ዕለት…

ፈረንሳይ የኔቶ ጦር በሆርሙዝ ሰርጥ እንዲሰማራ የቀረበውን ሀሳብ ውድቅ አደረገች

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 13፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ፈረንሳይ የሰሜን አትላንቲክ የጦር ቃልኪዳን ድርጅት (ኔቶ) በሆርሙዝ ሰርጥ እንዲሰማራ ከአባል ሀገራቱ የቀረበውን ሀሳብ ውድቅ አድርጋለች፡፡ የኔቶ ጦር ህብረት ከፍተኛ አዛዥ የሆኑት ጄነራል አሌክስ ግሪንኬዊች ኔቶ የሆርሙዝ ሰርጥን ደህንነት…

ምርጫው አካታች እንዲሆን የሚያስችሉ በርካታ ሥራዎች ተከናውነዋል – ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 13፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ አካታች እንዲሆን የሚያስችሉ በርካታ ሥራዎች ተከናውነዋል አሉ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ ሜላትወርቅ ኃይሉ፡፡ ቦርዱ ለምርጫው በተቋቋሙ ልዩ ምርጫ ጣቢያዎች የተመዘገቡ መራጮች በምርጫው ዕለት ድምጽ ስለሚሰጡበት…

ግብጽ የቀጣናው ሀገራት ልማት እንዳይሳካ ለዘመናት ትንኮሳ ስትፈጽም ቆይታለች – የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 13፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ግብጽ የቀጣናው ሀገራት የመልማት ፍላጎት እንዳይሳካ የምትፈጽመው ትንኮሳ አዲስ ክስተት ሳይሆን ለዘመናት የተከተለችው ስልት ነው አለ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር፡፡ የሚኒስቴሩ ቃል አቀባይ አምባሳደር ነቢያት ጌታቸው በዛሬው ዕለት በሰጡት መግለጫ፥…