Fana: At a Speed of Life!

ዶ/ር ኤርጎጌ ከተመድ የሴቶች ልዑካን ጋር ተወያዩ

አዲስ አበባ ፣ ግንቦት 21 ፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ)የኢፌዴሪ የሴቶች እና ማኅበራዊ ጉዳይ ሚኒስትር ዶክተር ኤርጎጌ ተሥፋዬ ከተመድ የሴቶች ልዑካን ቡዳን ጋር ተወያይተዋል፡፡ ዶክተር ኤርጎጌ ÷ የተመድ የሴቶች በኢትዮጵያ ተወካይ የሆኑትን ሴሲሊ ማካሩባ በቢሯቸው አግኝተው ተወያይተዋል፡፡…

ወልቂጤ ከነማ እና ኢትዮጵያ ቡና ተጋጣሚዎቻቸውን አሸነፉ

አዲስ አበባ ፣ ግንቦት 21 ፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በ26ኛ ሳምንት የቤትኪንግ ኢትዮጵያ ፕሪሚየርሊግ ወልቂጤ ከነማ እና ኢትዮጵያ ቡና ተጋጣሚዎቻቸውን አሸንፈዋል፡፡ ቀን 9 ሰዓት ላይ ኢትዮጵያ መድንን ያስተናገደው ወልቂጤ ከነማ 2 ለ 0 ማሸነፍ ችሏል፡፡ የወልቂጤ የማሸነፊያ ጎሎችን በእለቱ…

የኢትዮጵያ አየር መንገድ በአቢጃንና ኒውዮርክ መካከል የሚያደርገውን በረራ ጀመረ

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 21፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢትዮጵያ አየር መንገድ በአቢጃን እና ኒውዮርክ ከተሞች መካከል የሚያደርገውን ቀጥታ በረራ ጀምሯል፡፡ በረራው በዛሬው ዕለት በአቢጃን አውሮፕላን ማረፊያ በይፋ መጀመሩን የኢትዮጵያ አየር መንገድ መረጃ  ያመላክታል፡፡

አውስትራሊያ ለአፍሪካ ቀንድ እና የመካከለኛው ምስራቅ ሀገራት የ29 ሚሊየን ዶላር የሰብዓዊ ድጋፍ ይፋ አደረገች

አዲስ አበባ ፣ ግንቦት 21 ፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) አውስትራሊያ ኢትዮጵያን ጨምሮ በድርቅ ለተጎዱ የአፍሪካ ቀንድ እና የመካከለኛው ምስራቅ ሀገራት የ29 ሚሊየን ዶላር የሰብዓዊ ድጋፍ ይፋ ማድረጓን አስታውቃለች፡፡ በዛሬው እለት ይፋ የተደረገው ይህ የሰብዓዊ ድጋፍ የምግብ ዋስትና ቀውስ…

ቼልሲ ማውሪሲዮ ፖቼቲኖን አዲሱ የክለቡ አሰልጣኝ አድርጎ ሾመ

አዲስ አበባ ፣ ግንቦት 21 ፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የምዕራብ ለንደኑ ክለብ ቼልሲ ማውሪሲዮ ፖቼቲኖን አዲሱ የክለቡ አሰልጣኝ አድርጎ መሾሙን አስታውቋል፡፡ የቀድሞው የቶተንሃም እና የፓሪስ ሴንት ዠርሜን አሰልጣኝ ፖቼቲኖ ክለቡን በዋና አሰልጣኝነት ለመያዝ ሲነጋገሩ መቆየታቸው ይታወሳል።…

ተሽከርካሪ አምራቾች በየአመቱ 74 ሚሊየን ቶን ካርበን ዳይ ኦክሳይድ ያመነጫሉ – ግሪን ፒስ

አዲስ አበባ ፣ ግንቦት 21 ፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የዓለም ትላልቅ ተሽከርካሪ አምራች ኩባንያዎች በየአመቱ 74 ሚሊየን ቶን ካርበን ዳይ ኦክሳይድ እንደሚያመነጩ ዓለም አቀፉ የአካባቢ መብት ጥበቃ ተሟጋች ግሪን ፒስ አስታወቀ፡፡ ግሪን ፒስ ባወጣው ሪፖርት እንዳስታወቀው÷ መኪና አምራች…

በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ለመከላከያ ሰራዊት የድጋፍ ሰልፍ  ተካሄደ

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 20፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ለመከላከያ ሰራዊት የድጋፍ ሰልፍ ተካሂዷል። በአሶሳ ከተማ በተካሄደ የድጋፍ ሰልፍ ከተለያዩ አካባቢዎች የተውጣጡ የህብረተብ ክፍሎች ለሰራዊቱ ያላቸውን አለኝታነት ገልፀዋል። የሰልፉ ተሳታፊዎች መተኪያ የሌለውን ውድ…

በደቡብ ክልል “መከላከያ ሠራዊታችን ኢትዮጵያዊነታችን” በሚል መሪ ቃል የድጋፍ ሰልፍ ተካሄደ

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 20፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በደቡብ ክልል "መከላከያ ሠራዊታችን ኢትዮጵያዊነታችን'' በሚል መሪ ቃል የድጋፍ ሰልፍ ከማለዳው ጀምሮ ተካሂዷል፡፡ በአርባ ምንጭ እና ዲላ ከተማ በተካሄደ  ሰልፍ የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች እየተሳተፉ ሲሆን÷ አለኝታችን በሆነው ሠራዊታችን ላይ…

በኦሮሚያ ክልል ለመከላከያ ሰራዊት የድጋፍ ሰልፍ ተካሄደ

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 20፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በኦሮሚያ ክልል "መከላከያ ስራዊታችን ኢትዮጵያዊነታችን" በሚል መሪ ቃል  ለመከላከያ ሰራዊት የድጋፍ ሰልፍ ተካሄደ፡፡ ሰልፉ በክልሉ በሸገር ከተማ፣ ጅማ፣አዳማ፣ሻሸመኔ፣አምቦ፣ቢሾፍቱና በሌሎች ከተሞች ተካሂዷል፡፡ እየተካሄደ በሚገኘው ሰልፍ…

በሲዳማ ክልል ለመከላከያ ሰራዊት የድጋፍ ሰልፍ ተካሄደ

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 20፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በሲዳማ ክልል  ዜጎች ለመከላከያ ሠራዊት ያላቸውን ድጋፍ በታላቅ ሠላማዊ ሰልፍ ገልፀዋል። በሀዋሳ ከተማ ሰልፉ የተካሄደ ሲሆን ÷ከከተማዋ የተለያዩ ክፍለ ከተሞች የተውጣጡ  ነዋሪዎች  ለመከላከያ ሰራዊቱ ድጋፋቸውን ገልፀዋል ፡፡ ከህብረ…