Fana: At a Speed of Life!

ለቀጣዩ አረንጓዴ አሻራ መርሐ ግብር 76 ሺህ 192 ችግኝ ጣቢያዎች ወደ ስራ ገብተዋል

አዲስ አበባ፣ ጥር 2፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) ለቀጣዩ የአረንጓዴ አሻራ መርሐ ግብር 132 ሺህ 226 የችግኝ ጣቢያዎችን ወደ ስራ ለማስገባት ታቅዶ አሁን ላይ 76 ሺህ 192 ችግኝ ጣቢያዎች ሥራ መጀመራቸውን የግብርና ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡ የአረንጓዴ አሻራ መርሐ-ግብር ዓብይ ኮሚቴ የ2015/16…

በፕሪሚየር ሊጉ ድሬደዋ ከተማ ድል ቀንቶታል

አዲስ አበባ፣ ጥር 2፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 10ኛ ሳምንት የውድድር መርሐ ግብር ዛሬ ሁለት ጨዋታዎች ተካሂደዋል፡፡ ቀን 9 ሰዓት ላይ ድሬደዋ ከተማ እና ኢትዮጵያ መድን ያካሄዱት ጨዋታ 2 ለ 1 በሆነ ውጤት ተጠናቅቋል፡፡ የድሬደዋ ከተማን የማሸነፊያ ግቦች ቻርለስ…

በትግራይ ክልል በሁለት ቢሊየን ብር ወጪ የኤሌክትሪክ ኃይል ማሻሻያ ፕሮጀክት እየተካሄደ ነው

አዲስ አበባ፣ ጥር 2፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት በትግራይ ክልል በሁለት ቢሊየን ብር ወጪ የኤሌክትሪክ ኃይል ማሻሻያ ፕሮጀክት እያካሄደ መሆኑን አስታወቀ። በክልሉ ጊዜያዊ አስተዳደር የኤሌክትሪክ አገልግሎት ኮሙኒኬሽን ኃላፊ አቶ ግርማይ ግደይ እንደገለጹት÷ በፕሮጀክቱ…

የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር ለትግራይ ክልል የ5 ሚሊየን ብር ድጋፍ አደረገ

አዲስ አበባ፣ ጥር 2፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር በትግራይ ክልል በድርቅ ለተጎዱ ወገኖች የሚሆን የ5 ሚሊየን ብር ድጋፍ አድርጓል፡፡ የገቢዎች ሚኒስትር ወ/ሮ አይናለም ንጉሴ፣ የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስትር ኤርጎጌ ተስፋዬ (ዶ/ር) ጨምሮ ሌሎች ከፍተኛ…

የአምራች ኢንዱስትሪ ዘርፉን ለመደገፍ የጥናትና ምርምር ተቋማት የበኩላቸውን እንዲወጡ ተጠየቀ

አዲስ አበባ፣ ጥር 2፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የአምራች ኢንዱስትሪ ዘርፉን ለመደገፍ የጥናትና ምርምር ተቋማት የበኩላቸውን እንዲወጡ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳደር አቶ ጥላሁን ከበደ ጠየቁ፡፡ በአዲሱ የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ እና በተኪ ምርት ስትራቴጂ ዙሪያ ግንዛቤ ለመፍጠር የተዘጋጀ…

ትምህርት ሚኒስቴር ከደቡብ ኮሪያ ጋር በትምህርት ዘርፍ በትብብር ለመስራት ተስማማ

አዲስ አበባ፣ ጥር 2፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የትምህርት ሚኒስቴር ከደቡብ ኮሪያ ጊዮንግሳንግቡክ-ዶ ትምህርት ቢሮ ጋር በትምህርት መረጃ ልውውጥና ትብብር ዙሪያ በጋራ ለመስራት የሚያስችል የትብብር መግባቢያ ሰነድ ስምምነት ተፈራርሟል፡፡ ስምምነቱን የትምህርት ሚኒስትር ዴኤታ ወ/ሮ አየለች እሸቴ…

የግል ዳታ ጥበቃ አዋጅ የዲጂታል ኢኮኖሚውን ለማሳደግ ፋይዳው የጎላ ነው ተባለ

አዲስ አበባ፣ ጥር 1፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የግል ዳታ ጥበቃ ረቂቅ አዋጅ ለብዙ ዓመታት ማገልገል እንዲችል ታሳቢ ተደርጎ በቀጣይ የሚጸድቅ መሆኑን በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የሰው ኃብት ልማት፣ ስራ ስምሪትና ቴክኖሎጂ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ አስታወቀ፡፡ በዛሬው ዕለት በግል ዳታ ጥበቃ ረቂቅ አዋጅ…

አቶ ደስታ ሌዳሞ በኢንቨስትመንት ለባለሐብቶች የተሠጡ መሬቶች ያሉበትን ሁኔታ ጎበኙ

አዲስ አበባ፣ ጥር 1፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የሲዳማ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ በሐዋሳ ከተማ እንዲለሙ ለባለሐብቶች የተሰጡ የኢንቨስትመንት መሬቶች ያሉበትን ሁኔታ ተመልክተዋል፡፡ በጉብኝታቸው ወቅትም የኢንቨስትመንት መሬት ለታለመለት ዓላማ ሊውል እንደሚገባ ርዕሰ መስተዳድሩ…

የባሕር ኃይሉ በአሠራርና አደረጃጀት አቅሙን እያጠናከረ መምጣቱ ተመላከተ

አዲስ አበባ፣ ጥር 1፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የባሕር ኃይል በአሠራርና አደረጃጀት አቅሙን በይበልጥ እያጠናከረ መምጣቱን በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የውጪ ግንኙነት እና የሠላም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ አስታውቋል። ቋሚ ኮሚቴው በባሕር ኃይል ጠቅላይ መምሪያ ተገኝቶ ጉብኝት ካደረገ በኋላ ተቋሙ እስካሁን…

የኢትዮጵያና የሶማሊላንድ ስምምነት በጋራ የመልማት ቀጣናዊ ፖሊሲን እንደሚያጸና ተገለጸ

አዲስ አበባ፣ ጥር 1፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) ኢትዮጵያ ከሶማሊላንድ ጋር የተፈራረመችው የመግባቢያ ስምምነት ብሔራዊ ጥቅሟን የሚያስጠብቅና በቀጣናው የምትከተለውን በጋራ የመልማት ፖሊሲ የሚያጸና መሆኑን ሚኒስትሮች ገለጹ። የባህር በር የማግኘት ጉዳይ የህልውና እና የሉዓላዊነት ጉዳይ መሆኑን ሁሉም…