Fana: At a Speed of Life!

የአማርኛ ቋንቋ ትምህርት በሞስኮ ትምህርት ቤቶች ከመስከረም ጀምሮ ሊሰጥ ነው

አዲስ አበባ ፣ ግንቦት 16 ፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በሞስኮ ትምህርት ቤቶች ከመስከረም ጀምሮ አማርኛ ቋንቋ ማስተማር ሊጀመር መሆኑ ተገለጸ፡፡ ጉዳዩን አስመልክቶ የስፑትኒክ አለም አቀፍ የዜና አገልግሎት ድርጅት እና ሬዲዮ÷ በሩሲያ - አፍሪካ የኢኮኖሚ ትብብር ተስፋዎች ዙሪያ ውይይት አካሂዷል።…

የአሁኑ የአፍሪካ ህብረት የተመሰረተበት 60ኛ አመት በነገው እለት ይከበራል

አዲስ አበባ ፣ ግንቦት 16 ፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የቀድሞው የአፍሪካ አንድነት ድርጅት የአሁኑ የአፍሪካ ህብረት የተመሰረተበት 60ኛ አመት በነገው እለት ይከበራል። በፈረንጆቹ 1963 በ32 ነጻ ሀገራት የአፍሪካ አንድነት ድርጅት በሚል መመስረቱ ይታወሳል።…

“ከኮቪድ-19 ወረርሽኝ ያገኘነውን ት/ት በቀጣይ ሊከሰቱ የሚችሉ ወረርሽኞችን የመከላከልና ጠንካራ ምላሽ የመስጠት አቅምን መገንባት ላይ ማዋል ይገባል”- ዶ/ር…

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 16፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) “ከኮቪድ-19 ወረርሽኝ ያገኘነውን ትምህርት በቀጣይ ሊከሰቱ የሚችሉ ወረርሽኞችን የመከላከል፣ ፈጥኖ የመለየትና ጠንካራ ምላሽ የመስጠት አቅምን መገንባት ላይ ማዋል ይገባል” ሲሉ የጤና ሚኒስትሯ ዶክተር ሊያ ታደሰ ገለጹ፡፡ በስዊዘርላንድ ጄኔቫ…

በአቶ ደመቀ መኮንን የተመራ ልዑክ ለይፋዊ የሥራ ጉብኝት ቤጂንግ ገባ

አዲስ አበባ ፣ ግንቦት 16 ፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን የተመራ ልዑክ ለይፋዊ የሥራ ጉብኝት ቻይና ቤጂንግ ገባ። ልዑኩ ቤጂንግ ሲደርስ በቻይና የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የስራ ሃላፊዎች፣ በቻይና የኢትዮጵያ ኤምባሲ ሰራተኞች እና በቻይና…

የአረብ ሊግ ሀገራት በሕዳሴ ግድብ ላይ የሚያደርጉት ጣልቃ ገብነት ተቀባይነት የለውም- ጋዜጠኛና ተንታኝ ኩንጉ አል ማሃዲ አዳም

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 15፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ግንባታን በተመለከተ የአረብ ሊግ ሀገራት የሚያደርጉት ጣልቃ ገብነት ተቀባይነት የለውም ሲል ኡጋንዳዊው ጋዜጠኛና ተንታኝ ኩንጉ አል ማሃዲ አዳም አስተያየቱን ሰጠ፡፡ ጋዜጠኛ አል ማሃዲ የአረብ ሊግ ሀገራት የግብፅ ቃል…

አቶ ፈቃዱ ተሰማ በመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ መምህራን ላይ በደረሰው የትራፊክ አደጋ የተሰማቸውን ሃዘን ገለጹ

አዲስ አበባ ፣ ግንቦት 13፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በብልጽግና ፓርቲ የኦሮሚያ ክልል ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ፍቃዱ ተሰማ በመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ መምህራን ላይ በደረሰው የትራፊክ አደጋ የተሰማቸውን ሃዘን ገልጸዋል፡፡ በትናንትናው ዕለት ወደ ሻሸመኔ ካምፓስ ለማስተማር ሲጓዙ የነበሩ የመደ…

አትሌት ጸሃይ ገመቹ በሕንድ ባንጋሉር የ10 ኪ.ሜ የሩጫ ውድድር አሸነፈች

አዲስ አበባ ፣ ግንቦት 13፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) አትሌት ጸሃይ ገመቹ በህንድ ባንጋሉር በተካሄደ የ10 ኪሎ ሜትር የሩጫ ውድድር አሸነፈች፡፡ አትሌት ጸሃይ ርቀቱን 31 ደቂቃ ከ38 ሰከንድ በሆነ ሰዓት በመግባት ነው በቀዳሚነት ያጠናቀቀችው፡፡

አንቶኒዮ ጉተሬዝ ዓለም ለሁለት እንዳትከፈል ሲሉ አስጠነቀቁ

አዲስ አበባ ፣ ግንቦት 13፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሃፊ አንቶኒዮ ጉተሬዝ ዓለም ለሁለት እንዳትከፈል ሲሉ አስጠንቅቀዋል፡፡ የቡድን 7 አባል አገራት ከአሜሪካ ወይም ከቻይና ጋር በመሰለፍ ዓለምን በቀዝቃዛ ጦርነት ጎራዎች ከመከፋፈል እንዲቆጠቡ ዋና ፀሐፊው…

የዩኒቨርሲቲ መምህራንና ተማሪዎች የግብርና ሳይንስ አውደ ርዕይን ጎበኙ

አዲስ አበባ ፣ ግንቦት 13፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የዩኒቨርሲቲ መምህራንና ተማሪዎች በሳይንስ ሙዚየም የተዘጋጀውን የግብርና ሳይንስ አውደ ርዕይ ጎብኝተዋል። “ከቤተ-ሙከራ ወደ አዝመራ” በሚል መሪ ሃሳብ በሳይንስ ሙዚየም የተዘጋጀው የግብርና ሳይንስ ኢግዚቢሽን በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ…

ኮሚሽነር ሌሊሴ ነሜ በተባበሩት ዓረብ ኤምሬቶች ከሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ባለሃብቶች ጋር ተወያዩ

አዲስ አበባ ፣ ግንቦት 13፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢንቨስትመንት ኮሚሽን ኮሚኒሽነር ሌሊሴ ነሜ በተባበሩት ዓረብ ኤምሬቶች ከሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ባለሃብቶች ጋር ተወያይተዋል፡፡ በውይይታቸውም÷ ሌሊሴ ነሜ በኢንቨስትመንት ዘርፉ እንቅስቃሴ፣ በተወሰዱ የሕግ ማሻሻያዎች፣ የአደረጃጀትና የአሰራር…