Fana: At a Speed of Life!

በቱሪስት አገልግሎት ሰጭ ተቋማት ብሔራዊ የጥራት ማረጋገጥ ፕሮግራም ሊተገበር ነው

አዲስ አበባ፣ ጥር 3፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) ኢትዮጵያ ውስጥ በሚገኙ የቱሪስት አገልግሎት ሰጪ ተቋማት ብሔራዊ የአገልግሎት ጥራት ማረጋገጥ ፕሮግራም በቅርቡ እንደሚተገበር የቱሪዝም ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡ ጎብኚዎችን በሚያስተናግዱ እንደ ሆቴልና መሰል ተቋማት ጥራት እንዳይኖር ከሚያደርጉ ምክንያቶች…

ከ15 ሚሊየን ሔክታር በላይ ማሣ ላይ የነበረ ሰብል ተሰበሰበ

አዲስ አበባ፣ ጥር 3፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) እስከ ታኅሣስ 26 ቀን 2016 ዓ.ም ድረስ በ15 ሚሊየን 24 ሺህ 836 ሔክታር ማሣ ላይ የሚገኝ ሰብል መሰብሰቡን ግብርና ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡ የመኸር ሰብል መሰብሰብ በተጀመረባቸው ክልሎች እስከ ታኅሣስ 26 ቀን 2016 ዓ.ም ብቻ በባሕላዊ…

የሽግግር ፍትኅ የፖሊሲ ዝግጅት ላይ ውይይት ተካሄደ

አዲስ አበባ፣ ጥር 3፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በሽግግር ፍትኅ የፖሊሲዝግጅትና በጉዳዩ ላይ በቀጣይ መሥራት በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ውይይት መደረጉን የፍትኅ ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡ የፍትኅ ሚኒስትር ዴዔታ አቶ በላይሁን ይርጋ እና የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የሰብዓዊ መብት ከፍተኛ ኮሚሽነር ቢሮ…

በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ከ’የመደመር ትውልድ’ መጽሐፍ ሽያጭ የሚገነባው ሙዚየም ሥራ ተጀመረ

አዲስ አበባ፣ ጥር 3፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሥራ በሆነው ‘የመደመር ትውልድ’ መጽሐፍ ሽያጭ የሚገነባው “የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ሙዚዬም” የግንባታ ሥራ መጀመሩን የክልሉ መንግሥት አስታወቀ፡፡ ግንባታው በ18 ወራት እንዲጠናቀቅ የጊዜ ገደብ መቀመጡን…

ክልሉ ከ11 ቢሊየን ብር በላይ ካፒታል ላስመዘገቡ ባለሐብቶች ፈቃድ ሰጠ

አዲስ አበባ፣ ጥር 3፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በተያዘው በጀት ዓመት የመጀመሪያ ስድስት ወራት 11 ቢሊየን 490 ሚሊየን 458 ሺህ 249 ብር ላስመዘገቡ ባለሐብቶች ፈቃድ መስጠቱን የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል አስታወቀ፡፡ ፈቃዱ የተሰጠው በ26 የግብርና እና በሰባት የኢንዱስትሪ ዘርፎች…

በሕገ-ወጥ መንገድ ተንቀሳቅሰዋል የተባሉ ነጋዴዎች ከ1 ነጥብ 1 ሚሊየን ብር በላይ ተቀጡ

አዲስ አበባ፣ ጥር 3፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ንግድና ገበያ ልማት ቢሮ ባለፉት ስድስት ወራት ባካሄደው ክትትልና ቁጥጥር ከ980 በላይ በሆኑ የንግድ ተቋማት ላይ አስተዳደራዊ እርምጃ መውሰዱን አስታወቀ፡፡ የቢሮው ኃላፊ አቶ አጀሊ ሙሳ እንዳሉት÷ በሕገ-ወጥ መንገድ…

በበጎ ፈቃድ አገልግሎት ከ17 ነጥብ 5 ቢሊየን ብር በላይ ዋጋ ያለው ሥራ ተከናወነ

አዲስ አበባ፣ ጥር 2፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) ባለፉት ሥድስት ወራት በሀገር አቀፍ ደረጃ በበጎ ፈቃደኛ ወጣቶች 17 ቢሊየን 598 ሚሊየን 796 ሺህ 561 ብር ዋጋ ያለው ሥራ መከናወኑን የሴቶችና ማኅበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡ በተካሄደው የክረምት እና የበጋ ወቅት የበጎ ፈቃድ አገልግሎት…

ሀገር አቀፍ የጤናማ እናትነት ወር ተጀመረ

አዲስ አበባ፣ ጥር 1፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በሀገር አቀፍ ደረጃ ለ18ኛ ጊዜ የሚከበረው የጤናማ እናትነት ወር ዛሬ መጀመሩን ጤና ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡ የጤና ሚኒስትር ዶ/ር ሊያ ታደሰ ዛሬ በሰጡት መግለጫ እንዳስታወቁት÷ ወሩ የሚከበረው “ፍትሐዊነት፣ ተደራሽነት እና ጥራት ያለውን የቅድመ ወሊድ…

በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ መቻል ሲያሸንፍ ቅዱስ ጊዮርጊስ ነጥብ ጣለ

አዲስ አበባ፣ ጥር 1፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም በተካሄደው 10ኛ ሳምንት የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ መቻል ሲያሸንፍ ቅዱስ ጊዮርጊስ አቻ ተለያይቷል፡፡ 9፡00 ላይ ሐዋሳ ከተማን የገጠመው መቻል 2 ለ 1 አሸንፏል፡፡ የመቻልን ጎሎችም ምንይሉ ወንድሙ…

የወንጀል ድርጊቶችን ካሉበት ሆነው ለፖሊስ የሚያደርሱበት መተግበሪያ ሥራ ሊጀምር ነው ተባለ

አዲስ አበባ፣ ጥር 1፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የወንጀል ድርጊቶችን ዜጎች ካሉበት ሆነው ለፖሊስ የሚያደርሱበት የሞባይል መተግበሪያ በቅርቡ በአዲስ አበባ ሥራ እንደሚጀምር የኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽነር ጄኔራል ደመላሽ ገብረሚካኤል አስታወቁ፡፡ ፌዴራል ፖሊስ ከለውጡ በኋላ የሀገርንና የዜጎችን…