Fana: At a Speed of Life!

አዲሱ ዓመት የውስጥና የውጭ ፈተናዎችን አልፈን አዲስ ታሪክ የምናስመዘግብበት ይሆናል – የሰላም ሚኒስቴር

አዲስ አበባ፣ መስከረም 3፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) ኢትዮጵያ ፈተናዎች በገጠሟት ቁጥር እንደ ብረት ጠንክራ የምትወጣ በመሆኗ "አዲሱ ዓመት የውስጥና የውጭ ፈተናዎችን አልፈን አዲስ ታሪክ የምናስመዘግብበት እንደሚሆን የሰላም ሚኒስትር ዴኤታ ወርቅነሽ ብሩ ተናገሩ። የሰላም ሚኒስትር ዴኤታ…

የካማሽ ነዋሪዎች የትህነግ ተላላኪ በሆነው ታጣቂ ቡድን ላይ የማያዳግም ርምጃ እንዲወሰድ ጠየቁ

አዲስ አበባ፣ መስከረም 3፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የካማሽ ነዋሪዎች በክልሉ በሚንቀሳቀሰው ታጣቂ ሃይል ላይ መንግስት የማያዳግም ርምጃ እንዲወስድ ጠየቁ፡፡ ነዋሪዎቹ ጥያቄውን ያቀረቡት በዞኑ ካማሽ ከተማ ዛሬ ባካሄዱት ሠላማዊ ሰልፍ ላይ ነው፡፡…

የአፍሪካ ሕብረት ጊኒን ከአባልነት አገደ

አዲስ አበባ፣ ጳጉሜ 5፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) የአፍሪካ ሕብረት የፖለቲካ ጉዳዮች የሰላምና ደኅንነት መምሪያ በሃገሪቱ የተካሄደውን መፈንቅለ መንግሥት ተከትሎ ጊኒን ከዓባልነት ማገዱን አስታውቋል፡፡ ባሳለፍነው ሳምንት የጊኒው ፕሬዚዳንት አልፋ ኮንዴ በኮሎኔል ማማዲ ዱምቡያ በሚመራው…

ኮሚሽኑ በህክምና ላይ ላሉ የፖሊስ አባላት ስጦታ አበረከተ

አዲስ አበባ፣ ጰጉሜን 5፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) የፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽን አዲሱን ዓመት ምክንያት በማድረግ በፌደራል ፖሊስ ሪፈራል ሆስፒታል ህክምናቸውን እየተከታተሉ ላሉ የፖሊስ አባላት ስጦታ አበርክቷል፡፡ የፌደራል ፖሊስ ኮሚሽነር ጄኔራል ደመላሽ ገብረሚካኤልን ጨምሮ ሌሎች የተቋሙ…

የመከላከያ ዋር ኮሌጅ፣ የምስራቅ አፍሪካ የምክክር ጥናትና ትብብር ማዕከል እና የኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ በጋራ ለመሥራት ተስማሙ

አዲስ አበባ፣ ጳጉሜን 5፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) የመከላከያ ዋር ኮሌጅ፣ የምስራቅ አፍሪካ የምክክር ጥናትና ትብብር ማዕከል እና የኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ በጋራ ሀገራዊና በምስራቅ አፍሪካ ሰላምና ደህንነት ጉዳዮች ላይ ጥናትና ምርምር ለማድረግና ሀገራዊ፣ አለምአቀፍ ሲምፖዚየሞችንና የውይይት…

ከውጪ የገባው የምግብ ዘይት ለክልሎች እየተከፋፈለ ነው

አዲስ አበባ፣ ጳጉሜን 5፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) የዘመን መለዋጫ በዓልን አስመልክቶ የዘይት አቅርቦት ችግር እንዳይከሰተ ከውጪ የገባው የምግብ ዘይት ወደ ክልሎች እየተከፋፈል መሆኑን የንግድና ኢንዱስትሪ ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡ በሚኒስቴሩ የኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር…

2014 የድል እና የተስፋ ዓመት ይሆናል- የአማራ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን

አዲስ አበባ፣ ጳጉሜን 5፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) የአማራ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር ተኮላ አይፎክሩ አዲሱን ዓመት አስመልክተው የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል፡፡ በመልዕክታቸውም 2013 ለሀገራችን ብሎም ለክልላችን ፈታኝ አመት መሆኑን አስታውሰው መጭው ዓመት የድልና…

የጳጉሜን መጨረሻ የድል ቃል ኪዳን ብስራት ቀን በደማቅ ሥነ ስርዓት ተከበረ

አዲስ አበባ፣ ጳጉሜን 5፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) በአዲስ አበባ ከሁሉም ክፍለ ከተሞች የተወጣጡ ወጣቶችና የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች በተገኙበት አዲስ አበባ ተከብሯል፡፡ በመርሐ ግብሩ በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የማህበራዊ የመንግስት አገልግሎት ሰጪ ተቋማት አስተባባሪ አቶ ጃንጥራር…

ፈተናዎች ሁሉ በድል ተጠናቀው ፊታችንን ወደ ልማት የምናዞርበት እሩቅ እይደለም- አቶ ደስታ ሌዳሞ

አዲስ አበባ፣ ጳጉሜን 5፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) የሲዳማ ክልል ርዕሰ መስተዳደር አቶ ደስታ ሌዳሞ አዲሱን ዓመት አስመልክተው የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል። ርዕሰ መስተዳድሩ 2013 ዓ.ም 6ኛ ዙር ሀገር አቀፍ ምርጫ ዴሞክራሲያዊና ፍጹም ሠላማዊ በሆነ መንገድ መጠናቀቁ…

በዩኔስኮ የተቋቋመው ዓለም አቅፍ ኮሚሽን የመጨረሻ ሪፖርቱን አጸደቀ

አዲስ አበባ፣ ጳጉሜን 5፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) በፕሬዚዳንት ሣህለ ወርቅ ዘውዴ የሚመራው እና በዓለም የትምህርት የወደፊት እጣ ፈንታ ላይ ጥናት እንዲያደርግ በዩኔስኮ የተቋቋመው ዓለም አቀፍ ኮሚሽን የመጨረሻ ሪፖርቱን አጽድቋል። በፈረንጆቹ የፊታችን ጥቅምት ወር ለመንግሥታቱ ድርጅት…