Fana: At a Speed of Life!
Browsing Category

የሀገር ውስጥ ዜና

የመስቀል በዓል ማህበራዊ ግንኙነትን፣ አንድነትንና የጋራ እሴትን የሚያጎላ መሆን አለበት- ርእሰ መስተዳድር አወል አርባ

አዲስ አበባ፣ መስከረም 16፣ 2017 (ኤፍ ቢ ሲ) የመስቀል በዓልን የእምነቱ ተከታዮች ሲያከብሩ ማህበራዊ ግንኙነትን አንድነትና ወንድማማችነትን በሚያጠናክር የጋራ እሴታችን በሚያጎላ መልኩ መሆን እንዳለበት የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገለጹ፡፡ ርዕሰ መስተዳድሩ ለመስቀል በዓል…

የመስቀል ደመራ በዓል በድምቀት ተከብሮ ተጠናቀቀ

አዲስ አበባ፣ መስከረም 16፣ 2017 (ኤፍ ቢ ሲ) በዛሬው ዕለት በመላው ኢትዮጵያ የተከበረው የመስቀል ደመራ በዓል በድምቀት ተከበሮ መጠናቀቁን የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ አስታወቀ። የፌደራል ፖሊስ ከሌሎች የፀጥታና ደህንነት አካላት ጋር በመቀናጀት እና ቅድመ ዝግጅት በማድረግ በዕቅድ እየተመራ…

የመስቀል በዓልን ስናከብር ሰላምና እድገትን ዘላቂ ለማድረግ ቃል በመግባት ነው – አቶ ጌታቸው ረዳ

አዲስ አበባ፣ መስከረም 16፣ 2017 (ኤፍ ቢ ሲ) የመስቀል በዓልን ስናከብር ሰላም፣ ልማትና እድገት ዘላቂ ለማድረግ ቃል በመግባት ነው ሲሉ የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ርዕሰ መስተዳድር አቶ ጌታቸው ረዳ ገለጹ። በትግራይ ክልል የመስቀል በዓል በተለያዩ አካባቢዎች በድምቀት ተከብሯል።…

የመስቀል ደመራ በዓል በተለያዩ ከተሞች እየተከበረ ነው

አዲስ አበባ፣ መስከረም 16፣ 2017 (ኤፍ ቢ ሲ) የመስቀል ደመራ በዓል በተለያዩ ከተሞች በድምቀት እየተከበረ ይገኛል፡፡ በዓሉ በጅማ ከተማ በደማቅ እየተከበረ ሲሆን የእምነቱ ተከታዮች እና በከተማዋ ከሚገኙ 17 ደብራት የተውጣጡ የተለያዩ የሰንበት ት/ቤት ተማሪዎች እንዲሁም አባቶች በዓሉን…

የመስቀል ደመራ በዓል በተለያዩ ክልሎች እየተከበረ ነው

አዲስ አበባ፣ መስከረም 16፣ 2017 (ኤፍ ቢ ሲ) የመስቀል ደመራ በዓል የተለያዩ ክልሎች በመከበር ላይ ይገኛል፡፡ በዓሉ በጋምቤላ ከተማ በርካታ ምዕምናን በተገኙበት በድምቀት እየተከበረ ሲሆን በአከባበር ስነ ስርዓቱ የዕምነቱ አባቶች፣ ምዕመናንና የመንግስት የሥራ ኃላፊዎች መታደማቸውን የክልሉ…

በዓሉን ፍቅራችንና አንድነታችን በማጎልበትና በመደጋገፍ ልናከብረው ይገባል – ከንቲባ ከድር ጁሃር

አዲስ አበባ፣ መስከረም 16፣ 2017 (ኤፍ ቢ ሲ) የመስቀል ደመራ በዓልን ስናከበር ፍቅራችንንና አንድነታችንን በማጎልበትና በመደጋገፍ ሊሆን ይገባል ሲሉ የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ከድር ጁሃር ገለጹ። ከንቲባው የመስቀል ደመራ በዓልን አስመልክቶ ባስተላለፉት የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት፤…

መስቀል የትዕግሥት፣ የዕርቅና የሰላም ምልክት መሆኑን ማሰብ ያስፈልጋል – አቶ አረጋ ከበደ

አዲስ አበባ፣ መስከረም 16፣ 2017 (ኤፍ ቢ ሲ) መስቀል የትዕግሥት፣ የዕርቅና የሰላም ምልክት መሆኑን ማሰብ ያስፈልጋል ሲሉ የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ ገለጹ፡፡ ርዕሰ መስተዳድሩ የመስቀል በዓልን አስመልክተው ባስተላለፉት የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት፤ ቅዱስ መስቀል ከኃጢአት…

አምባሳደር ታዬ አጽቀሥላሴ ከግሪክና ሴራሊዮን አቻዎቻቸው ጋር ተወያዩ

አዲስ አበባ፣ መስከረም 16፣ 2017 (ኤፍ ቢ ሲ) የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ታዬ አጽቀሥላሴ ኢትዮጵያ ከግሪክ እና ሴራሊዮን ጋር ያላትን ግንኙነት በሚያጠናክሩ ጉዳዮች ዙሪያ ከሁለቱ ሀገራት አቻዎቻቸው ጋር ተወያይተዋል። ሚኒስትሩ ከግሪኩ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጊኦርጎስ ጀርፐትራይተስ ጋር…

ቻይና ለኢትዮጵያ በቴክኒክና ሙያ ዘርፍ የምታደርገውን ድጋፍ አጠናክራ እንደምትቀጥል ገለጸች

አዲስ አበባ፣ መስከረም 16፣ 2017 (ኤፍ ቢ ሲ) ቻይና ለኢትዮጵያ በቴክኒክና ሙያ ዘርፍ የምታደርገውን ድጋፍ አጠናክራ እንደምትቀጥል በኢትዮጵያ የቻይና አምባሳደር ቼን ሃይ ገለጹ፡፡ የስራና ክሎት ሚኒስትር ሙፈሪያት ካሚል በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ፥ በኢትዮጵያ የቻይና አምባሳደር ከሆኑት ቼን…

የመስቀል ደመራ በዓል በመስቀል አደባባይ እየተከበረ ነው

አዲስ አበባ፣ መስከረም 16፣ 2017 (ኤፍ ቢ ሲ) የመስቀል ደመራ በዓል በአዲስ አበባ መስቀል አደባባይ እየተከበረ ይገኛል፡፡ በበዓሉ ላይ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ፓትርያርክ ብጹዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ፣ ፕሬዚዳንት ሣኅለወርቅ ዘውዴ፣ የባህልና ስፖርት ሚኒስትር ሸዊት…