Browsing Category
ስፓርት
የቻምፒዮንስ ሊግ ፍጻሜ ወደ ፖርቶ ተዛወረ
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 5፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) በቼልሲ እና በማንቼስተር ሲቲ መካከል የሚካሄደው የቻምፒዮንስ ሊግ የፍጻሜ ጨዋታ ወደ ፖርቹጋል መዛወሩ ተገለጸ፡፡
በፍጻሜው ጨዋታ 12 ሺህ የሚደርሱ የሁለቱ ቡድን ደጋፊዎች ይታደማሉ ተብሏል፡፡
ቀደም ሲል ጨዋታው በቱርክ ኢስታንቡል አታቱርክ…
በፕሪሚየር ሊጉ ሰበታ ከተማ በመጨረሻዎቹ ደቂቃዎች ላይ ባስቆጠሩት ግብ ሀድያ ሆሳዕናን አሸነፉ
አዲስ አበባ ፣ ግንቦት 4 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ)በቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ሰበታ ከተማ በመጨረሻዎቹ ደቂቃዎች ላይ ባስቆጠሩት ግብ ሀድያ ሆሳዕናን አሸንፈዋል።
የሰበታ ከተማን የማሸነፊያ ግቦች ኦሴ ማዊሊ በ45ኛውና 62ኛው ደቂቃዎች ላይ በፍፁም ቅጣት ምት ሲያቆጥር፤ የማሸነፊያውን ግብ…
በፕሪሚየር ሊጉ ድሬ ዳዋ ከተማ ሲያሸንፍ አዳማና ጅማ አባ ጅፋር ወራጅ መሆናቸው ተረጋግጧል
አዲስ አበባ ፣ ግንቦት 4 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) ቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ ድሬ ዳዋ ከተማ ወልቂጤ ከተማን 2 ለ 1 አሸነፈ።
የድሬ ዳዋን ማሸነፊያ ግቦች ሪችሞንድ አይንጎ በ45ኛው እና በ90ኛው ደቂቃዎች ላይ ሲያስቆጥር ፤ ወልቂጤን ከሽንፈት ያልታደገች ግብ አብዱልከሪም ወርቁ…
በመዲናዋ ከ700 ሚሊየን ብር በላይ ወጪ የተደረገባቸው 42 የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎች በዚህ ዓመት አገልግሎት ይሰጣሉ
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 4፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከ700 ሚሊየን ብር በላይ ወጪ የተደረገባቸው 42 የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎች ግንባታቸው ተጠናቆ በተያዘው ዓመት አገልግሎት መስጠት እንደሚጀምሩ የአዲስ አበባ ስፖርት ኮሚሽን አስታወቀ።
ኮሚሽኑ የስፖርት ማዘውተሪያ…
በፕሪሚየር ሊጉ ወላይታ ዲቻና ጅማ አባጅፋር አቻ ተለያዩ
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 3፣ 2013 (ኤፍቢሲ) በቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 23ኛ ሳምንት ወላይታ ዲቻና ጅማ አባጅፋር አቻ ተለያይተዋል፡፡
በመጀመሪያ አጋማሽ ጅማ አባጅፋር መሪ መሆን የሚያስችለውን ግብ በፕሪንስ ዋኦንጎ አማካኝነት በ39 ደቂቃ ላይ አስቆጥሯል፡፡
ሆኖም ወላይታ ዲቻ…
አትሌት ጉዳፍ ፀጋይ በ10 ሺህ ሜትር ፈጣን ሰዓት በማስመዝገብ አሸነፈች
አዲስ አበባ ፣ግንቦት 2 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ )ኢትዮጵያዊቷ አትሌት ጉዳፍ ፀጋይ በ10 ሺህ ሜትር የመጀመሪያ የውድድር ተሳትፎዋ ፈጣን ሰዓት በማስመዝገብ አሸንፋለች፡፡
በፖርቹጋል በተደረገ የፌርናንዳ ሪቤይሮ ጎልድ በ10 ሺህ ሜትር ሴቶች ውድድር አትሌት ጉዳፍ ፀጋይ በመጀመሪያ ተሳትፎዋ…
በፕሪሚየር ሊጉ ቅዱስ ጊዮርጊስ ባህርዳር ከተማን አሸነፈ
አዲስ አበባ ፣ ሚያዝያ 30 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) በቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ቅዱስ ጊዮርጊስ ባህርዳር ከተማን 2 ለ 0 አሸነፈ።
ጨዋታው ከእረፍት በፊት 0 ለ 0 ተጠናቆ የነበረ ቢሆንም ቅዱስ ጊዮርጊሶች ከእረፍት መልስ ባስቆጠሯቸው ግቦች ሶስት ነጥብ ማግኘት ችለዋል።
የቅዱስ…
በፕሪሚየር ሊጉ ፋሲል ከነማ ወልቂጤን አሸነፈ
አዲስ አበባ ፣ ሚያዝያ 30 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) በቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ረፋድ ላይ አንድ ጨዋታ ተካሂዷል፡፡
የሊጉን ሻምፒዮን ፋሲል ከነማን ከወልቂጤ ከተማ ያገናኘው ጨዋታ በፋሲል ከነማ 1 ለ 0 አሸናፊነት ተጠናቋል፡፡
ሽመክት ጉግሳ ለከፋሲል ከነማ የማሸነፊያ ጎሏን…
በፕሪሚየር ሊጉ ሀዋሳ ከተማ ሀድያ ሆሳዕናን 3 ለ 0 አሸነፈ
አዲስ አበባ ፣ ሚያዝያ 29 ፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) በቤት ኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ሀዋሳ ከተማ ሀድያ ሆሳዕናን 3 ለ 0 አሸነፈ።
ከደመወዝ ጋር በተያያዝ የሀድያ ሆሳዕና በርካታ ተጫዋቾች ባለባቸው ቅሬታ ከአዲስ አበባ ወደ ሀዋሳ ሳይጓዙ በመቅረታቸው ቡድኑ ሳይሟላ…
ፋሲል ከነማ የ2013ዓ.ም የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ሻምፒዮን መሆኑን አረጋገጠ
አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 28፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) በ22ኛ ሳምንት የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ኢትዮጵያ ቡና እና ወላይታ ዲቻ 0 ለ 0 በሆነ አቻ ውጤት ተለያይተዋል።
ዛሬ ከሰዓት በሃዋሳ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም የተደረገው ጨዋታ ኢትዮጵያ ቡናን ከወላይታ ዲቻ…