Fana: At a Speed of Life!
Browsing Category

ዓለምአቀፋዊ ዜና

ሰሜን ኮሪያ ሁለት ሚሳኤሎች አስወነጨፈች

አዲስ አበባ ፣ የካቲት 23 ፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ) ሰሜን ኮሪያ ሁለት ሚሳኤሎች ማስወንጨፏን የሃገሪቱ ጦር አስታወቀ። ሚሳኤሎቹ ከሃገሪቱ ምስራቃዊ የባህር ዳርቻ ወደ ጃፓን ባህር የተወነጨፉ ናቸው። የአሁኑ ሙከራ የፈረንጆቹ 2020 ከገባ በኋላ የመጀመሪያዋ ሲሆን፥ ባለፈው ህዳር ወር ላይ…

በአየርላንድ፣ ኢኳዶር፣ አርሜኒያና ኳታር አዲስ የኮሮና ቫይረስ ተጠቂዎች ተገኙ

አዲስ አበባ ፣ የካቲት 22፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የኮሮና ቨይረስ ስርጭት እየጨመረ የመጣ ሲሆን፥ በአየርላንድ፣ኢኳዶር ፣አርሜኒያ እና ኳታር አዲስ ቫይረሱ ተጠቂዎች መገኘታቸው ተገልጿል። መነሻውን ከቻይና ውሃን ግዛት አድርጎ የተቀሰቀሰው የኮሮና ቫይረስ በርካታ ሃገሮችን እያዳረሰ ይገኛል።…

በደቡብ ኮሪያ በአንድ ቀን 594 አዳዲስ የኮሮና ቫይረስ ተጠቂዎች ተገኙ

አዲስ አበባ፣ የካቲት 21፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) በደቡብ ኮሪያ በአንድ ቀን ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው አዳዲስ የኮሮና ቫይረስ ተጠቂዎች ተገኙ። የሃገሪቱ የበሽታ መቆጣጠሪያና መከላከያ ማዕከል እንዳስታወቀው፥ በአንድ ቀን ብቻ 594 አዳዲስ የቫይረሱ ተጠቂዎች ተገኝተዋል። ይህም እስካሁን በቫይረሱ…

ናይጀሪያ የኮሮና ቫይረስ ተጠቂ የተገኘባት ሶስተኛዋ አፍሪካዊ ሀገር ሆናለች

አዲስ አበባ ፣ የካቲት 20 ፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) ናይጀሪያ በኮሮና ቫይረስ የተጠቃ ሰው የተገኘባት ሶስተኛዋ አፍሪካዊ ሀገር ሆናለች። የቫይረሱ ተጠቂ የሆነው ግለሰብ ጣሊያናዊ ዜግነት ያለው ሲሆን፥ ናይጄሪያ ውስጥ የሚሰራና ከሶስት ቀን በፊት ከሚላን ወደ ሌጎስ የመጣ ነው ተብሏል።…

በኢድሊብ በተፈጸመ የአየር ጥቃት 33 የቱርክ ወታደሮች ለህልፈት ተዳረጉ

አዲስ አበባ፣ የካቲት 20፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) ቱርክ በሶሪያ ኢድሊብ ግዛት የበሽር አላሳድ ወታደሮች በፈጸሙት ጥቃት 33 ወታደሮቿ መገደላቸውን አስታወቀች። ወታደሮቹ በአየር ጥቃት መገደላቸውን አንድ የሃገሪቱ ከፍተኛ ባለስልጣን ተናግረዋል። ጥቃቱን ተከትሎም ቱርክ የሶሪያ መንግስት…

የደቡብ አፍሪካ የደህንነት ሚኒስትር ስልክ ተጠለፈ

አዲስ አበባ ፣ የካቲት 19 ፣ 2012(ኤፍ ቢ ሲ) የደቡብ አፍሪካ የደህንነት ሚኒስትር አያንዳ ድሎድሎ እና የምክትላቸው ስልክ መጠለፉ ተሰምቷል፡፡ የሃገሪቱ መርማሪዎች የደህንነት ሚኒስትሯ ስልክ እና የሌሎች ባርደረቦቻቸው ስልክ እንዴት እንደተጠለፈ በማጣራት ላይ መሆናቸው ተገልጿል። መረጃ…

የቱኒዚያ አዲሱ መንግስት የመተማመኛ ድምጽ አገኘ

አዲስ አበባ ፣ የካቲት 19 ፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ) የቱኒዚያ አዲሱ መንግስት በፓርላማው የመተማመኛ ድምጽ አገኘ። ፓርላማው ባለፈው ወር ማብቂያ ላይ በሃገሪቱ ፕሬዚዳንት ካይስ ሳይድ የቀረበውን የኤልዬስ ፋክህፋክህን ጠቅላይ ሚኒስትርነት ሹመትም አጽድቆታል። በጠቅላይ ሚኒስትሩ የተመሰረተው…

ሳዑዲ ዓረቢያ ወደ መካ የሚደረጉ ጉዞዎችን አገደች

አዲስ አበባ ፣ የካቲት 19 ፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ) ሳዑዲ ዓረቢያ ወደ መካ የሚደረጉ ጉዞዎች ላይ እገዳ መጣሏን አስታወቀች። የጉዞ እገዳው ሐይማኖታዊ እና መደበኛ ተጓዦችን የሚያካትት ሲሆን፥ የስርጭት አድማሱን እያሰፋ ካለው የኮሮና ቫይረስ ጋር የተያያዘ መሆኑንም አስታውቃለች። ይህን…

አሜሪካ እና ደቡብ ኮሪያ በኮሮና ቫይረስ ስጋት ዓመታዊ የጋራ ወታደራዊ ልምምዳቸውን አራዘሙ

አዲስ አበባ፣ የካቲት 19፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ) አሜሪካ እና ደቡብ ኮሪያ በኮሮና ቫይረስ ስጋት ምክንያት በየዓመቱ የሚያካሂዱትን የጋራ ወታደራዊ ልምምድ አራዝመዋል። ዋሽንግተን እና ሴኡል ዓመታዊ የጋራ ወታደራዊ ልምምዳቸውን ያራዘሙት በሀገራቱ መከላከያ ሰራዊት ውስጥ በኮሮና ቫይረስ የተያዙ…

ሶማሊያ የ330 ሚሊየን ዶላር እዳ ስረዛ ተደረገላት

አዲስ አበባ ፣ የካቲት 19 ፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ) ዓለም አቀፉ የገንዘብ ተቋም (አይ ኤም ኤፍ) ለሶማሊያ የ330 ሚሊየን ዶላር እዳ ስረዛ መደረጉን አስታወቀ። እንደ ተቋሙ ገለጻ 100 አበዳሪዎች ለምስራቅ አፍሪካዊቷ ሃገር የዕዳ ስረዛውን ለማድረግ ተስማምተዋል። የዕዳ ስረዛው ሶማሊያ…