Fana: At a Speed of Life!

የእሳትአደጋው ከባድ ጉዳት ከማድረሱ በፊት በቁጥጥር ስር ውሏል-ወ/ሮ አዳነች አቤቤ

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 25 ፣2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ)በአዲስ አበባ አዋሬ ገበያ አካባቢ የተነሳው የእሳት አደጋ ከባድ ጉዳት ከማድረሱ በፊት በቁጥጥር ስር መዋሉን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ አዳነች አቤቤ አስታወቁ በአዲስ አበባ የተከሰተውን የእሳት ቃጠሎ አስመልክተው ምክትል…

መከላከያ ሀገሪቱን ለመታደግ እየወሰደው ያለውን ዕርምጃ የጋምቤላ የክልል እንደሚደግፍ አቶ ዑሞድ ኡጁሉ አስታወቁ

አዲስ አበባ ፣ ጥቅምት 25 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢፌዴሪ መከላከያ ሰራዊት ሀገሪቱን ለመታደግ እየወሰደው ያለውን ዕርምጃ የጋምቤላ የክልል እንደሚደግፍ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ ዑሞድ ኡጁሉ አስታወቁ። ሕወሓት በሠራዊቱ ላይ ያደረሰው ጥቃት የሀገር ክህደት ወንጀል መሆኑን ርዕሰ መስተዳድሩ…

ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ለተመራቂ ተማሪዎች ገብተው ሪፖርት እንዲያደርጉ ያቀረቡት ጥሪ ለጊዜው እንዲቆም ተደረገ

አዲስ አበባ ፣ጥቅምት 25 ፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ለተመራቂ ተማሪዎች ከጥቅምት 23 ፣2013 ጀምሮ ገብተው ሪፖርት እንዲያደርጉ ያቀረቡት ጥሪ ለጊዜው እንዲቆም መደረጉን የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር አስታወቀ። ሚኒስቴሩ ለኢቢሲ በላከው መግለጫ ለሁሉም…

የሀገር መከላከያ ሰራዊት የተቃጣበትን ጥቃት በመመከት የህዝቦችን ደህንነትና የሀገሪቱን ሉዓላዊነት በማስጠበቅ ሃላፊነቱን እየተወጣ ነው -ሚኒስቴሩ

አዲስ አበባ ፣ጥቅምት 25 ፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) በኢፌዴሪ የሀገር መከላከያ ሰራዊት ላይ በህወሃት የተቃጣበትን ጥቃት በመመከትና በማክሸፍ የሀገሪቱን ሉዓላዊነት በማስጠበቅ ሃላፊነቱን እየተወጣ መሆኑን የመከላከያ ሚኒስቴር አስታወቀ። ከትናንት ምሽት ጀምሮ በኢፌዴሪ የሀገር…

አብንና ኢዜማ ሕወሓት በትግራይ ክልል በሚገኘው የመከላለከያ ሠራዊት ላይ የከፈተውን ጥቃት እንደሚያወግዙ አስታወቁ

አዲስ አበባ ፣ ጥቅምት 25 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ (አብን) እና የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትህ(ኢዜማ) ሕወሓት በትግራይ ክልል በሚገኘው የኢፌዴሪ መከላለከያ ሠራዊት ላይ የከፈተውን ጥቃት እንደሚያወግዙ አስታወቁ፡፡ ፓርቲዎቹ ዛሬ ባወጡት መግለጫ…

የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በኢትዮጵያ ወቅታዊ ጉዳይ ዙሪያ ለዲፕሎማቲክ ማህበረሰቡ ማብራሪያ ሰጠ

አዲስ አበባ ፣ጥቅምት 25 ፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ዲና ሙፍቲ በኢትዮጵያ ስላለው ወቅታዊ ጉዳይ ዙሪያ ለዲፕሎማቲክ ማህበረሰቡ ማብራሪያ በዛሬው ዕለት ሰጥተዋል። አምባሳደር ዲና ለዲፕሎማቲክ ማህበረሰቡ እና መቀመጫቸውን አዲስ አበባ ላደረጉ…