ስፓርት
የአውሮፓ ዋንጫ የጥሎ ማለፍ ጨዋታዎች ከዛሬ ጀምሮ ይካሄዳሉ
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 22፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በ17ኛው የአውሮፓ ዋንጫ የጥሎ ማለፍ መርሐ ግብር ከዛሬ ሰኔ 22 ጀምሮ እስከ ሰኔ 25 ቀን 2016 ዓ.ም ይከናወናሉ።
በጀርመን አስተናጋጅነት እየተካሄደ ባለው ውድድር ጥሎ ማለፉን የተቀላቀሉ ብሔራዊ ቡድኖች ብርቱ ፉክክር ያደርጋሉ ተብሎ ይጠበቃል።
በዚህም ዛሬ ምሽት አንድ ሰዓት ላይ ስዊዘርላንድ ከዩሮ 2020 ሻምፒዮኗ ጣሊያን ጋር ትገናኛለች።
የሁለቱ አሸናፊ ቡድን በሩብ ፍጻሜው ከእንግሊዝና ስሎቫኪያ አሸናፊ ጋር የሚገናኝ ይሆናል።
ጣሊያን በምድብ ማጣሪያው ከምድብ ሁለት ስፔንን…
Read More...
ኢትዮጵያ መድን ሀድያ ሆሳዕናን አሸነፈ
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 21፣ 2016 (ኤፍቢ ሲ) በ29ኛ ሣምንት የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ኢትዮጵያ መድን ሀድያ ሆሳዕናን 1 ለ 0 አሸንፏል፡፡
የመድንን ብቸኛ የማሸነፊያ ጎልም ወገኔ ገዛኸኝ በሁለተኛው አጋማሽ ከመረብ አሳርፏል፡፡
ለኢትዮጵያ አትሌቲክስ ልዑክ አባላት ከ1 ነጥብ 3 ሚሊየን ብር በላይ ሽልማት ተበረከተ
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 21፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በ23ኛው የአፍሪካ አትሌቲክስ ሻምፒዮና ለተካፈለው የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ልዑካን ቡድን አባላት ከ1 ነጥብ 3 ሚሊየን ብር በላይ የማበረታቻ ሽልማት ተበረከተላቸው፡፡
በካሜሩን ዱዋላ በተካሄደው 23ኛው የአፍሪካ አትሌቲክስ ሻምፒዮና ተካፍሎ ትናንት አዲስ አበባ ለገባው የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ልዑክ ዛሬ በግዮን ሆቴል ዕውቅናና…
በአፍሪካ አትሌቲክስ ሻምፒዮና 4ኛ ደረጃ በመያዝ ላጠናቀቀው የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ልዑክ አቀባበል ተደረገለት
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 20፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በ23ኛው የአፍሪካ አትሌቲክስ ሻምፒዮና 4ኛ ደረጃ በመያዝ ላጠናቀቀው የኢትዮጵያ አትሌቲክስ የልዑካን ቡድን አቀባበል ተደርጎለታል።
በ23ኛው የአፍሪካ አትሌቲክስ ሻምፒዮና ኢትዮጵያ 5 ወርቅ፣ 4 የብርና 1 የነሐስ ሜዳልያ በማግኘት አጠናቅቃለች።
በካሜሩን ዱዋላ አስተናጋጅነት በተካሔደውና ከ27 ሀገራት በላይ የተውጣጡ 2…
የማንችስተር ዩናይትድ የቀድሞ ኮከብ ተጫዋች ሉዊስ ናኒ ወደ ኢትዮጵያ ሊመጣ ነው
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 20፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የፖርቹጋል ብሔራዊ ቡድንና የማንችስተር ዩናይትድ ተጫዋች የነበረው ሉዊስ ናኒ ወደ ኢትዮጵያ እንደሚመጣ የመቻል ስፖርት ክለብ አስታወቋል፡፡
ሉዊስ ናኒ የመቻል ስፖርት ክለብ 80ኛ ዓመት የምስረታ በዓል ላይ በክብር እንግድነት ለመታደም ነው ወደ ኢትዮጵያ የሚመጣው፡፡
የመቻል ስፖርት ክለብ ቦርድ ሰብሳቢ ሰይፉ ጌታሁን…
በፕሪሚየር ሊጉ ባህርዳር ከተማ እና ሀዋሳ ከተማ አቻ ተለያዩ
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 20፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በ29ኛ ሳምንት የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ባህርዳር ከተማ እና ሀዋሳ ከተማ አንድ አቻ ተለያይተዋል፡፡
በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም በተደረገው ጨዋታ ለባህር ዳር ከተማ ፍቅረ ሚካኤል አለሙ ሲያስቆጥር ለሃዋሳ ከተማ ደግሞ አሊ ሱሌማን በፍፁም ቅጣት ምት ኳሷን ከመረብ አገናኝቷል፡፡
የ29ኛ ሳምንት መርሃ ግብሮች…
በአውሮፓ ዋንጫ የምድብ ጨዋታዎች ምን አዳዲስ የታሪክ ክስተቶች ተስተዋሉ?
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 20፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የአውሮፓ ዋንጫ የምድብ ጨዋታዎች አስገራሚ ክስተቶችን አስተናግደው ትናንት ምሽት በተደረጉ ጨዋታዎች ተጠናቀው ወደ ጥሎ ማለፉ የሚገቡ 16 ቡድኖች ተለይተው ታውቀዋል።
ለ13 ቀናት በተደረጉ የምድብ ጨዋታዎች ጥሩ ስብስብ ያላት ክሮሺያ ሳትጠበቅ ከምድብ ስትሰናበት ምስራቅ አውሮፓዊቷ ዩክሬን 4 ነጥብ እያላት ከምድብ ሳታልፍ…