ስፓርት
በፕሪሚየር ሊጉ የላንክሻዬር ደርቢ በኦልድትራፎርድ ይደረጋል
አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 26፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ማንቼስተር ዩናይትድ ከሊቨርፑል የሚያደርጉት የላንክሻዬር ደርቢ ጨዋታ ዛሬ 12 ሠዓት ላይ ይደረጋል፡፡
ቀደም ሲል ከተደረጉ ሥድስት የላንክሻዬር ደርቢ ጨዋታዎች ሊቨርፑል አምስቱን እንዲሁም ማንቼስተር ዩናይትድ አንድ ጊዜ አሸንፈዋል፡፡
ግብፃዊው አጥቂ ሞሐመድ ሳላህ በኦልድትራፎርድ መረብ ላይ 14 ጎሎችን ሲያስቆጥር÷ እንግሊዛዊው ማርከስ ራሽፎርድ ደግሞ ሰባት ጎሎችን በሊቨርፑል መረብ ላይ ማሳረፍ ችሏል፡፡
በማንቼስተር ዩናይትድ በኩል ሜሰን ማውንት በጉዳት ምክንያት…
Read More...
ኢትዮጵያ ከአፍሪካ 1ኛ ከዓለም 2ኛ ሆና ሻምፒዮናውን አጠናቀቀች
አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 26፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በፔሩ ሊማ በተካሄደው የዓለም ከ20 ዓመት በታች አትሌቲክስ ሻምፒዮና ኢትዮጵያ ከአፍሪካ አንደኛ ከዓለም ደግሞ ሁለተኛ ደረጃን በመያዝ አጠናቀቀች፡፡
የኢትዮጵያ ከ20 ዓመት በታች አትሌቲክስ ብሔራዊ ቡድን በውድድሩ÷ 6 የወርቅ፣ 2 የብር እና 2 የነሐስ በአጠቃላይ 10 ሜዳሊያዎችን አስገኝቷል፡፡
በዚሁ መሠረት አትሌት…
አርሰናል ስተርሊንግን፤ ቼልሲ ደግሞ ሳንቾን አስፈረሙ
አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 25፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በአውሮፓ የክረምቱ የተጫዋቾች የዝውውር መስኮት ማጠቃለያ ላይ አርሰናል ራሂም ስተርሊንግን፤ ቼልሲ ደግሞ ጃዶን ሳንቾን አስፈርመዋል።
አርሰናል የቸልሲውን ራሂም ስተርሊን በአንድ ዓመት የውሰት ውል ማስፈረሙ ተገልጿል።
እንዲሁም በክረምቱ የዝውውር መስኮት የነቃ እንቅስቃሴ የነበረው ቼልሲ የማንቼስተር ዩናይትዱን የክንፍ…
ዛሬ ፍጻሜውን በሚያገኘው የአትሌቲክስ ሻምፒዮና ኢትዮጵያውያን የሚጠበቁባቸው ሶስት ውድድሮች ይካሄዳሉ
አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 25፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በፔሩ ሊማ ሲካሄድ በነበረውና ዛሬ ምሽት ፍጻሜውን በሚያገኘው የዓለም ከ20 ዓመት በታች አትሌቲክስ ሻምፒዮና ኢትዮጵያውያን አትሌቶች የሚጠበቁባቸው ሶስት ውድድሮች ይካሄዳሉ።
በዚህም በ1 ሺህ 500 ሜትር ሴቶች የፍፃሜ ውድድር አትሌት ሳሮን በርሀ እና ፅጌ ተሾመ ሌሊት 7:00 ላይ ለሜዳሊያ ብርቱ ፉክክር ያደርጋሉ ተብሎ…
ከ20 ዓመት በታች የዓለም ሻምፒዮና ኢትዮጵያ የምትሳተፍባቸው 4 የፍጻሜ ውድድሮች ዛሬ ይካሄዳሉ
አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 24፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በፔሩ ሊማ እየተካሄደ በሚገኘው የዓለም ከ20 ዓመት በታች አትሌቲክስ ሻምፒዮና ኢትዮጵያውያን አትሌቶች የሚሳተፉባቸው አራት የፍጻሜ ውድድሮችበዛሬው ዕለት ይካሄዳሉ፡፡
በዚህ መሰረትም አትሌት ሕይወት አምባውና አትሌት ብርሃን ሙሉ የሚሳተፉበት የሴቶች 10 ሺህ ሜትር ርምጃ ውድድር ከምሽቱ 12 ሰዓት ከ25 ላይ ይካሄዳል፡፡…
አትሌት ሲምቦ ዓለማየሁ በሴቶች 3 ሺህ ሜትር መሰናክል ለኢትዮጵያ የወርቅ ሜዳሊያ አስገኘች
አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 24፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በፔሩ ሊማ እየተካሄደ በሚገኘው ከ20 ዓመት በታች የዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና አትሌት ሲምቦ ዓለማየሁ በሴቶች 3 ሺህ ሜትር መሰናክል ለኢትዮጵያ የወርቅ ሜዳሊያ አስገኘች።
አትሌት ሲምቦ በ9 ደቂቃ ከ12 ሰከንድ 71 ማይክሮ ሰከንድ በመግባት የሻምፒዮናውን ክብረወሰን በመስበር ጭምር ነው ማሸነፍ የቻለችው፡፡
በውድድሩ ላይ…
ክርስቲያኖ ሮናልዶ የአውሮፓ እግር ኳስ ማህበር ልዩ ተሸላሚ ሆነ
አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 23፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ የምንግዜም ከፍተኛ ጎል አስቆጣሪው ክርስቲያኖ ሮናልዶ የአውሮፓ እግር ኳስ ማህበር ልዩ ተሸላሚ መሆን ችሏል።
ሽልማቱ ይፋ የተደረገው ዛሬ በሞናኮ በተካሄደው የአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ የምድብ ድልድል ስነ ስርዓት ላይ ሲሆን፥ በአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ ያሳለፈው ስኬታማ ጊዜ ለሽልማቱ እንዳበቃውም…