ስፓርት
የመቻል ስፖርተኞች በስፖርቱ ዘርፍ የኢትዮጵያ አደራ አለባቸው – ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ
አዲስ አበባ፣ ሕዳር 23፣ 2017 (ኤፍ ቢ ሲ) የመቻል ስፖርተኞች በስፖርቱ ዘርፍ ከተቋም ባለፈ የኢትዮጵያ አደራ አለባቸው ሲሉ የኢፌዴሪ ጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ ገለጹ፡፡
ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ በናይጀሪያ አቡጃ በመላው አፍሪካ የጦር ሃይሎች ስፖርት ፌስቲቫል ተካፋይ ለነበረው የመቻል አትሌቲክስ ቡድን አቀባበል አድርገዋል።
መቻል ስፖርት ክለብ የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት ሞዴል መሆኑን ጠቅሰው፤ በሀገራችንም በመዝገብ የተረጋገጠ ብዙ ታሪክ ያለው የአንጋፋ ስፖርተኞች መፍለቂያ ነው ብለዋል፡፡…
Read More...
አትሌት ታምራት ቶላ እና አትሌት ሲምቦ አለማየሁ የአመቱ ምርጥ አትሌቶች ተባሉ
አዲስ አበባ፣ ሕዳር 22፣ 2017 (ኤፍ ቢ ሲ) አትሌት ታምራት ቶላ ከስታዲየም ውጭ የዓመቱ ምርጥ የጎዳና ላይ ውድድር አትሌት ሽልማትን አሸንፏል፡፡
አትሌት ታምራት ቶላ በፓሪስ ኦሎምፒከ አዲስ ክብረ ወሰን በማሻሻል በማሸነፍ ለሀገሩ ብቸኛውን ወርቅ ሜዳሊያ ማስገኘቱ ይታወሳል።
ሌላኛዋ አትሌት ሲምቦ አለማየሁ ደግሞ የዓመቱ ምርጥ ታዳጊ አትሌት ሽልማትን ማሸነፏን የዓለም…
ቼልሲ እና ማንቼስተር ዩናይትድ ተጋጣሚዎቻቸውን አሸነፉ
አዲስ አበባ፣ ሕዳር 22፣ 2017 (ኤፍ ቢ ሲ) በ13ኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየርሊግ ቼልሲ እና ማንቼስተር ዩናይትድ ተጋጣሚዎቻቸውን አሸንፈዋል፡፡
ቀን 10 ሰዓት ከ30 በስታምፎርድ ብሪጅ አስቶንቪላን ያስተናገደው ቼልሲ በኒኮላስ ጃክሰን ፣ ኤንዞ ፈርናንዴዜ እና ኮል ፓልመር ጎሎች 3 ለ 0 አሸንፏል፡፡
በተመሳሳይ ሰዓት በተደረገ ሌላ ጨዋታ ማንቼስተር ዩናይትድ…
በቫሌንሺያ ማራቶን አትሌት መገርቱ ዓለሙ አሸነፈች
አዲስ አበባ፣ ሕዳር 22፣ 2017 (ኤፍ ቢ ሲ) ዛሬ ረፋድ ላይ በተካሄደው የቫሌንሺያ ሴቶች ማራቶን ውድድር አትሌት መገርቱ ዓለሙ አሸናፊ ሆናለች።
አትሌቷ ርቀቱን ለማጠናቀቅ 2 ሠዓት ከ16 ደቂቃ ከ49 ሰከንድ ወስዶባታል፡፡
እንዲሁም አትሌት ጥሩዬ መስፍን ሦስተኛ ደረጃን ስትይዝ፥ ዑጋንዳዊቷ ስቴላ ቼሳንድ ሁለተኛ ሆና አጠናቅቃለች፡፡
በቫሌንሺያ ማራቶን አትሌት ደረሳ ገለታ 2ኛ ደረጃን ያዘ
አዲስ አበባ፣ ሕዳር 22፣ 2017 (ኤፍ ቢ ሲ) በስፔን ቫሌንሺያ በተካሄደው የወንዶች ማራቶን ውድድር አትሌት ደረሳ ገለታ ሁለተኛ ደረጃን ይዞ አጠናቀቀ፡፡
ኬንያውዩ አትሌት ሴባስቲያን ሳዌ ውድድሩን በቀዳሚነት ሲያጠናቅቅ÷ ሌላኛው ኬንያውይ አትሌት ዳኒኤል ማቴኮ ሦስተኛ ሆኗል፡፡
እንዲሁም አትሌት ጪምዴሳ ደበሌ 6ኛ እና የአምናው የውድድሩ አሸናፊ አትሌት ሲሳይ ለማ…
በወዳጅነት ዐደባባይ ከ10 ሺህ በላይ ተሳታፊዎች በተገኙበት የአካል ብቃት እንቅስቃሴ ተካሄደ
አዲስ አበባ፣ ሕዳር 22፣ 2017 (ኤፍ ቢ ሲ) በኢትዮጵያ የሚከበረውን የፀረ-ሙስና ቀን ምክንያት በማድረግ በወዳጅነት ዐደባባይ ከሁሉም የመዲናዋ ክፍለ ከተሞች የተወጣጡ ከ10 ሺህ በላይ ተሳታፊዎች በተገኙበት የአካል ብቃት እንቅስቃሴ ተካሂዷል፡፡
የአካል ብቃት እንቅስቃሴው የተካሄደው÷ “ወጣቶችን ያማከለ የፀረ-ሙስና ትግል የነገን ስብዕና ይገነባል” በሚል መሪ ሐሳብ…
ሊቨርፑል ከማንቼስተር ሲቲ የሚያደርጉት ፍልሚያ ይጠበቃል
አዲስ አበባ፣ ሕዳር 22፣ 2017 (ኤፍ ቢ ሲ) የ13ኛ ሣምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ-ግብሮች ሲቀጥሉ ምሽት 1 ሠዓት ላይ ሊቨርፑል በአንፊልድ ከማንቼስተር ሲቲ ጋር የሚያደርጉት ፍልሚያ በጉጉት ይጠበቃል፡፡
ሊጉን በ31 ነጥቦች እየመራ የሚገኘው የመርሲሳይዱ ክለብ ሊቨርፑል ውኃ ሰማያዊዮቹን ያሸንፋል የሚሉ የቅድመ-ጨዋታ አስተያየቶችም ተበራክተዋል፡፡
በሌላ…