Fana: At a Speed of Life!

ስፓርት

ቱርክ ጆርጂያን 3 ለ 1 አሸነፈች

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 11፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) ምሽት 1ሰዓት ላይ በተደረገ የአውሮፓ ዋንጫ የምድብ 6 ጨዋታ ቱርክ ጆርጂያን 3 ለ 1 በሆነ ውጤት አሸንፋለች፡፡ የቱርክን የማሸነፊያ ጎሎች መርት ሙልደር ፣ አርዳ ጉለርና ሙሀመድ ከሪም አክቱር ኮግሉ ሲያስቆጥሩ ጆርገስ ሚካታድዝ ደግሞ ለጆርጂያ አስቆጠሯል፡፡ ከዚሁ ምድብ ፖርቱጋልና ቼክ ሪፐብሊክ ጨዋታቸውን ምሽት 4 ሰዓት ላይ የሚያደርጉ ይሆናል፡፡
Read More...

የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ የጨዋታ መርሐ-ግብር ይፋ ሆነ

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 11፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ የ2024/25 የውድድር ዓመት የጨዋታ መርሐ-ግብር በዛሬው ዕለት ይፋ ተደርጓል። በዚሁ መሠረት የ2024/25 የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ በፈረንጆቹ ነሐሴ 16 ቀን 2024 ማንቼስተር ዩናይትድ ከፉልሃም በሚያደርጉት ጨዋታ የሚጀመር ይሆናል፡፡ በሊጉ የመጀመሪያ ሣምንት ጨዋታዎችም÷ የ2023/2024…

ፖርቹጋል የምትጠበቅበት የአውሮፓ ዋንጫ ጨዋታ ዛሬ ይካሄዳል

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 11፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በ17ኛው የ2024 የአውሮፓ ዋንጫ ጨዋታ ፖርቹጋል ከቼክ ሪፐብሊክ የሚያደርጉት ፍልሚያ ይጠበቃል፡፡ የመጀመሪያው ዙር የምድብ ማጣሪያ የመጨረሻ ጨዋታዎች ዛሬ ይካሄዳሉ፡፡ በዚህም በምድብ ሥድስት የሚገኙት ቱርክ እና ጆርጂያ ምሽት 1 ሠዓት ላይ የሚጫወቱ ሲሆን÷ ጨዋታውን የማሸነፍ ዕድሉ ለቱርክ ተሰጥቷል፡፡ እንዲሁም…

በአውሮፓ ዋንጫ ጨዋታ ሮማንያ ዩክሬንን 3 ለ 0 አሸነፈች

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 10፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) እየተካሄደ በሚገኘው የአውሮፓ ዋንጫ ጨዋታ ቀደም ብሎ የአሸናፊነት ግምት ያልተሰጣት ሮማንያ ዩክሬንን 3 ለ 0 ረትታለች፡፡ ኳስ ተቆጣጥሮ በመጫወት ብልጫ የነበራት ዩክሬን÷ ስታንቺዩ በ29ኛው፣ ማሪን በ53ኛው እና ድራጉስ በ57ኛው ደቂቃ ከመረብ ባሳረፏቸው ጎሎች ሽንፈት አስተናግዳለች፡፡ ውጤቱን ተከትሎም ሮማንያ ሦስት…

በአውሮፓ ዋንጫ ፈረንሳይ ከኦስትሪያ የሚያደርጉት ጨዋታ ይጠበቃል

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 10፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) 17ኛው የ2024 የአውሮፓ ዋንጫ መርሐ-ግብሮች ሲቀጥሉ ዛሬ ሦስት ጨዋታዎች ይደረጋሉ፡፡ በዚሁ መሠረት በምድብ አምስት የሚገኙት ሮማንያ እና ዩክሬን ቀን 10 ሠዓት እንዲሁም ቤልጂየም ከስሎቫኪያ ምሽት 1 ሠዓት ላይ ይጫወታሉ፡፡ በሌላ በኩል በምድብ አራት የሚገኙት ኦስትሪያ እና ፈረንሳይ ምሽት 4 ሠዓት ላይ የሚያደርጉት…

ዴንማርክና ስሎቬኒያ አቻ ተለያዩ

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 9፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በጀርመን አስተናጋጅነት እየተካሄደ በሚገኘው 17ኛው የ2024 የአውሮፓ ዋንጫ ጨዋታ ዴንማርክ እና ስሎቬኒያ 1 ለ 1 በሆነ አቻ ውጤት ተለያይተዋል፡፡ የዴንማርክን ጎል ክርስቲያን ኤሪክሰን በ17ኛው ደቂቃ ከመረብ ማሳረፍ ችሏል፡፡ የስሎቬኒያን የአቻነት ጎል ጃንዛ በ77ኛው ደቂቃ ላይ አስቆጥሯል። ቀደም ብሎ 10 ሠዓት…

በሩዋንዳ በተካሄደ የቦክስ ውድድር ኢትዮጵያ 2 የወርቅ ሜዳሊያ አገኘች

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 10፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በሩዋንዳ ኪጋሊ በተካሄደ የቦክስ ውድድር ኢትዮጵያ ሁለት የወርቅ ሜዳሊያ አግኝታለች፡፡ በውድድሩ ገነት ፀጋዬ በ57 ኪሎ ግራም የሩዋንዳ ተጋጣሚዋን በብቃት በማሸነፍ የወርቅ ሜዳሊያና የውድድሩ ድንቅ እንስት ቡጢኛ በመባል የዋንጫ ተሸላሚ ሆናለች፡፡ በወንዶች ምድብ ደግሞ በ63 ነጥብ 5 ኪሎ ግራም ኢ/ር አብርሃም ዓለም…