Fana: At a Speed of Life!

ስፓርት

መድፈኞቹ በፕሪሚየር ሊጉ ሁለተኛ ድላቸውን አስመዘገቡ

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 18፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የሰሜን ለንደኑ ክለብ አርሰናል አስቶንቪላን በሜዳው 2 ለ 0 በማሸነፍ የፕሪሚየር ሊጉን ሁለተኛ ድል አስመዝግቧል፡፡ ጎሎቹንም ትሮሳርድ በ67ኛው እንዲሁም ፓርቴ በ77ኛው ደቂቃ ከመረብ አሳርፈዋል፡፡ በቅድመ ጨዋታ የማሸነፍ ግምት የተሰጠው አርሰናል ኳስ ተቆጣጥሮ በመጫወት ብልጫ ወስዷል፡፡ በመጀመሪያው ሣምንት የፕሪሚየር ሊጉ ጨዋታዎች አርሰናል ዎልቭስን 2 ለ 0 ሲረታ÷ አስቶንቪላ ዌስትሃምን 2 ለ 1 ማሸነፉ ይታወሳል፡፡ ዛሬ ቀንና አመሻሽ ላይ በተካሄዱ የፕሪሚየር ሊጉ ሁለተኛ…
Read More...

ቶተንሃም፣ ኖቲንግሃም ፎረስት፣ ፉልሃም፣ ማንቼስተር ሲቲና ዌስትሃም ተጋጣሚዎቻቸውን አሸነፉ

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 18፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ሁለተኛ ሣምንት ጨዋታዎች ቶተንሃም ሆትስፐር፣ ዌስትሃም፣ ኖቲንግሃም ፎረስት፣ ፉልሃም እና ማንቼስተር ሲቲ ተጋጣሚዎቻቸውን አሸንፈዋል፡፡ በዚህም መሠረት÷ ቶተንሃም ኤቨርተንን 4 ለ 0፣ ዌስትሃም ክሪስታል ፓላስን 2 ለ 0፣ ኖቲንግሃም ፎረስት ሳውዝ ሃምተንን 1 ለ 0፣ ፉልሃም ሌስተር ሲቲን 2 ለ 1…

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የዑጋንዳውን ኤስ ሲ ቪላ በማሸነፍ ወደ ቀጣዩ ዙር አለፈ

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 18፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የካፍ ሻምፒየንስ ሊግ የቅድመ ማጣሪያ የመልስ ጨዋታውን በአበበ ቢቂላ ስታዲየም ከዑጋንዳው ክለብ ኤስ ሲ ቪላ ጋር ያደረገው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የወንዶች እግር ኳስ ቡድን አንድ አቻ አጠናቅቋል። ጎሎቹን ሱሌይማን ሀሚድ በ64ኛው ደቂቃ ለንድ ባንክ እንዲሁም ለኤስ ሲ ቪላ ፓትሪክ ካካንዴ በ74ኛው ደቂቃ አስቆጥረዋል፡፡…

በፕሪሚየር ሊጉ ብራይተን ማንቼስተር ዩናይትድን አሸነፈ

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 18፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ሁለተኛ ሣምንት ጨዋታ ማንቼስተር ዩናይትድን በሜዳው ያስተናገደው ብራይተን 2 ለ 1 አሸንፏል፡፡ የብራይተንን ጎሎች ዳኒ ዌልቤክ በ32ኛው እና ፔድሮ በ95ኛው ደቂቃ ከመረብ ሲያሳርፉ÷ የቀያይ ሰይጣኖቹን ብቸኛ ጎል አማድ ዲያሎ በ60ኛው ደቂቃ አስቆጥሯል፡፡ በፕሪሚየር ሊጉ የመጀመሪያ ሣምንት…

በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ተጠባቂ ጨዋታዎች ዛሬ ይደረጋሉ

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 18፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ የሁለተኛ ሳምንት መርሐ ግብር ዛሬ ሰባት ጨዋታዎች ይደረጋሉ። ማንቸስተር ዩናይትድ ወደ አሜክስ ስታዲየም አቅንቶ ቀን 8፡30 ብራይተንን የሚገጥምበት ጨዋታ የዕለቱ ቀዳሚ መርሐ ግብር ነው። ምሽት 1፡30 በቪላ ፓርክ አርሰናልን ከአስቶን ቪላ የሚያገናኘው ጨዋታ ደግሞ ከፍተኛ ፉክክር እንደሚደረግበት…

የዓለም ከ20 ዓመት በታች የአትሌቲክስ ሻምፒዮና የኢትዮጵያ ልዑክ ወደ ፔሩ አቀና

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 18፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በፈረንጆቹ ከነሐሴ 27 እስከ 31 ቀን በፔሩ ሊማ ለሚካሄደው የዓለም ከ20 ዓመት በታች የአትሌቲክስ ሻምፒዮና የኢትዮጵያ ልዑክ ወደ ፔሩ አቅንቷል። የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ፕሬዚዳንት ረዳት ኮሚሽነር አትሌት ደራርቱ ቱሉና የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ዮሐንስ እንግዳ በቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን…

በሉዛን ዳይመንድ ሊግ የ3 ሺህ ሜትር ሴቶች ውድድር ድርቤ ወልተጂ አሸነፈች

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 17፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በስዊዘርላንድ በተካሄደው የሉዛን ዳይመንድ ሊግ የ3 ሺህ ሜትር ሴቶች ውድድር አትሌት ድርቤ ወልተጂ የቦታውን አዲስ ሪከርድ በማስመዝገብ አሸንፋለች፡፡ አትሌት ድርቤ ወልተጂ ርቀቱን በ8 ደቂቃ 21 ሰከንድ ከ50 ማይክሮ ሰከንድ በማጠናቀቅ ነው በቀዳሚት ማሸነፍ የቻለችው፡፡ ሌላኛዋ አትሌት ጽጌ ገብረሰላማ የራሷን ምርጥ…