Fana: At a Speed of Life!

ስፓርት

አትሌት ለተሰንበት ግደይ የዓለም አቀፍ የአትሌቲክስ የስፖርታዊ ጨዋነት ሽልማት አሸናፊ ሆነች

አዲስ አበባ፣ ሕዳር 29፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) ኢትዮጵያዊቷ አትሌት ለተሰንበት ግደይ የዓለም አቀፍ የአትሌቲክስ የስፖርታዊ ጨዋነት ሽልማት አሸናፊ ሆናለች፡፡ በዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና ቡዳፔስት ላይ በተካሄደ የ10 ሺህ ሜትር ሩጫ ውድድር ትውልደ ኢትዮጵያዊት የሆነችው እና በአሁኑ ጊዜ ለሆላንድ የምትሮጠው ሲፋን ሐሰን በሩጫ ወቅት መውደቋ ይታወሳል፡፡ ይህን ተከትሎም አትሌት ለተሰንበት ግደይ አትሌቷ ውድድሯን ጨርሳ ስተገባ እንዴት እንደሆነች በመጠየቅና አይዞሽ በማለቷ መልካም ተግባር ስለፈጸምሽ የዓለም አትሌቲክስ የስፖርታዊ ጨዋነት…
Read More...

በፕሪሚየር ሊጉ መቻል እና ባህር ዳር ከተማ ድል ቀናቸው

አዲስ አበባ ፣ ሕዳር 28 ፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በሰባተኛው ሳምንት የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር በዛሬው እለት ሁለት ጨዋታዎች ተደርገዋል።   ቀደም ብሎ በተካሄደ ጨዋታ መቻል ከአዳማ ከተማ ተገናኝተዋል።   አዳማ ከተማ ጨዋታውን በቢኒያም አይተን ጎል 1 ለ 0 መምራት ቢችልም ተከታትለው በተቆጠሩበት ሁለት ጎሎች 2 ለ 1…

በፕሪሚየር ሊጉ ወላይታ ድቻ እና ወልቂጤ ከተማ ድል ቀናቸው

አዲስ አበባ፣ ሕዳር 27፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 7ኛ ሳምንት መርሐ ግብር ሁለት ጨዋታዎች ተካሂደዋል፡፡ 9 ሰዓት ላይ በተካሄደ የመጀመሪያው ጨዋታ ወልቂጤ ከተማ ሀምበርቾን 1 ለ 0 በሆነ ውጤት አሸንፏል፡፡ የወልቂጤ ከተማ ግብን አሜ መሐመድ ያስቆጠረ ሲሆን÷በዚህም ቡድኑ ተከታታይ ድልን አሳክቷል። እንዲሁም 12 ሠዓት ላይ በተካሄደ ጨዋታ…

የአትሌት ድርቤ ወልተጂ የ1 ማይል ርቀት ክብረወሰን ፀደቀ

አዲስ አበባ፣ ሕዳር 27፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) አትሌት ድርቤ ወልተጂ የአንድ ማይል ርቀት ክብረወሰን በአለምአቀፉ  አትሌቲክስ እውቅና አግኝቷል። ለመጀመሪያ ጊዜ በላቲቪያ ሪጋ በ1 ማይል ርቀት በተካሄደው የሴቶች ውድድር አትሌት ድርቤ ወልተጂ በ4 ደቂቃ ከ20 ሰከንድ ከ98 ማይክሮ ሰከንድ  በመግባት የርቀቱን ክብረወሰን ማሻሻሏ የሚታወስ ነው።…

የብራዚሉ ክለብ ሳንቶስ ከ111 ዓመት በኋላ ወደ ታችኛው ዲቪዚዮን መውረዱ አነጋጋሪ ሆኗል

አዲስ አበባ፣ ሕዳር 27፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በርካታ ከዋክብቶችን ያፈራው የብራዚሉ ክለብ ሳንቶስ ከ111 ዓመት በኋላ ወደ ታችኛው ዲቪዚዮን መውረዱ ደጋፊዎችን አስቆጥቷል፡፡ ሳንቶስ የክለቡ ወርቃማ ዘመን በተባለው  1950ዎቹ እና 60ዎቹ 12 የሀገራዊ ውድድር ክብሮችን፣6 የሊግ ውድድር ዋንጫዎችን እንዲሁም 2 የኮፓሊቨርታዶርስ ዋንጫዎችን ማሳካት ችሏል፡፡ ይሁን…

ኢትዮጵያ በውሃ ዋና ስፖርት ውድድር በታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ ሁለት የወርቅ ሜዳሊያ አገኘች

አዲስ አበባ፣ ሕዳር 26፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) ኢትዮጵያ በውሃ ዋና ስፖርት ውድድር በታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ ሁለት የወርቅ ሜዳሊያ አገኘች፡፡ የኢትዮጵያ ውሃ ዋና ስፖርት ብሔራዊ ቡድን በሩዋንዳ ኪጋሊ በተካሄደው 8ኛው የዞን 3 አፍሪካ ውሃ ዋና ሻምፒዮና በማስተርስ ዋና ውድድር በታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ ሁለት የወርቅ ሜዳሊያ አስመዝግቧል፡፡ ኢትዮጵያ በዞን 3 የአፍሪካ…

የብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ቀንን በማስመልከት በጂግጂጋ የጎዳና ላይ የሩጫ ውድድር ተካሄደ

አዲስ አበባ፣ ሕዳር 25፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) 18ኛውን የብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ቀን በዓልን በማስመልከት በጂግጂጋ ከተማ የ5 ኪሎ ሜትር የጎዳና ላይ ሩጫ ውድድር ተካሂዷል፡፡ በወንዶች በተደረገው የሩጫ ውድድር ከጅግጅጋ አትሌቲክስ ፕሮጀክት የተወከለው አትሌት አሕመድ መሐመድ 1ኛ፣ ከጅግጅጋ አትሌቲክስ ፕሮጀክት የተወከሉት አትሌት በረከት መሐመድ 2ኛ እንዲሁም…