ስፓርት
የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን ከግብፅ አቻው ጋር ጨዋታውን ያደርጋል
አዲስ አበባ፣ ጳጉሜን 3፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን በአፍሪካ ዋንጫ ማጣርያ ከግብፅ አቻው ጋር ዘሬ ምሽት ጨዋታውን ያደርጋል፡፡
አስቀድሞ ከአፍሪካ ዋንጫ ተሳትፎ ውጪ መሆኑን ያረጋገጠው ብሔራዊ ቡድኑ÷ መርሐ ግብሩን ለማከናነወን ከቀናት በፊት ካይሮ መግባቱ ይታወሳል፡፡
የዋሊያዎቹ ጊዜያዊ አሰልጣኝ ዳንኤል ገብረማሪያም ከጨዋታው አስቀድመው በሰጡት መግለጫ ÷ የብሄራዊ ቡድኑ አባላት በሙሉ ጤንነት ላይ እንደሚገኙ ገልፀዋል፡፡
“ለአፍሪካ ዋንጫው ማለፍ ባንችልም ÷ ጨዋታው ለቀጣይ የዓለም ዋንጫ ማጣርያ እና ለቻን ማጣርያ…
Read More...
የ2023ቱ የባሎንዶር ኮከብ ተጫዋቾች ዝርዝር ይፋ ሆነ
አዲስ አበባ፣ ጳጉሜን 2፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የ2023ቱ የባሎንዶር ኮከብ ተጫዋቾች ዝርዝር ትላንት ምሽት ይፋ ተደርጓል፡፡
30 ተጫዋቾች በቀረቡበት የባሎዶር የኮከቦች ዕጩ ዝርዝር ውስጥ የአምስት ጊዜ አሸናፊው ክርስቲያኖ ሮናልዶ ከፈረንጆቹ 2003 ወዲህ ለመጀመሪያ ጊዜ አለመካተቱ ተገልጿል፡፡
በአንጻሩ የዓለም ዋንጫ አሸናፊው ሊዮኔል ሜሲ እና በማንቼስተር ሲቲ ድንቅ…
አሰልጣኝ ፍሬው ኃይለገብርኤል ለ26 ተጫዋቾች ጥሪ አቀረቡ
አዲስ አበባ፣ ጳጉሜን 1፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢትዮጵያ ሴቶች ብሔራዊ ቡድን አሰልጣኝ ፍሬው ኃይለገብርኤል ለ26 ተጫዋቾች ጥሪ አቅርበዋል፡፡
ብሔራዊ ቡድኑ በ2024 የአፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያ ከቡሩንዲ ጋር መስከረም 9 እና 15 ቀን 2016 ዓ.ም ለሚያደርጋቸው የመጀመሪያ ዙር ጨዋታዎች ዝግጅት ለማድረግ ነው ለ26 ተጫዋቾች ጥሪ የቀረበው፡፡
በዚሁ መሠረት በግብ…
የማንቼስተር ዩናይትድ ዋጋ በ500 ሚሊየን ፓውንድ ዝቅ ማለቱ ተገለፀ
አዲስ አበባ፣ ጳጉሜን 1፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የላንክሻየሩ ክለብ ማንቼስተር ዩናይትድ የሽያጭ ዋጋው በ500 ሚሊየን ፓውንድ ዝቅ ማለቱ ተገልጿል፡፡
የክለቡ ዋጋ በአሜሪካው የኒዎርክ የአክሲዮን ሽያጭ በ500 ሚሊየን ፓውንድ ወይም በ628 ነጥብ 5 ሚሊየን ዶላር ዝቅ ማለቱ ተጠቅሷል፡፡
ክለቡ በአርሰናል ከተሸነፈ በኋላ መልበሻ ክፍል ውስጥ አለመግባባቶች ተፈጥረው…
ዋልያዎቹ ለአፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያ ጨዋታ ካይሮ ገብተዋል
አዲስ አበባ፣ ጳጉሜን 1፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን አባላት ከግብፅ አቻቸው ጋር የአፍሪካ ዋንጫ ማጣርያ መርሐ ግብርን ለማከናወን ካይሮ ገብተዋል፡፡
የብሄራዊ ቡድኑን ተጫዋቾች እና አመራሮችን የያዘው ልዑክ ከ3 ሰዓታት በላይ በረራ በኋላ ካይሮ በሰላም መግባቱን የፌዴሬሽኑ መረጃ ያመላክታል፡፡
ሁለቱ ቡድኖች ቀደም ሲል ባደረጉት ጨዋታ ዋሊያዎቹ በዳዋ…
ለአትሌቲክስ ልዑካን ቡድኑ የሽልማት ስነ-ስርዓት በብሔራዊ ቤተ-መንግስት ተካሄደ
አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 28፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በ19ኛው የዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና ለተሳተፈው የአትሌቲክስ ልዑክ ቡድን የዕውቅናና የሽልማት ስነ-ስርዓት በብሔራዊ ቤተ-መንግስት ተካሂዷል።
በዕውቅናና የሽልማት ስነ-ስርዓርቱ የኢፌዲሪ ፕሬዚዳንት ሣኅለወርቅ ዘውዴ፣ የባህልና ስፖርት ሚኒስትር ቀጀላ መርዳሳን ጨምሮ የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ፕሬዝዳንት ረዳት ኮሚሽነር…
አትሌት ለተሰንበት የሴቶች 5ሺህ ሜትር ሩጫ 4ኛውን ፈጣን ሰዓት አስመዘገበች
አዲሰ አበባ፣ ነሐሴ 28፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) አትሌት ለተሰንበት ግደይ የሴቶች 5ሺህ ሜትር ሩጫ 4ኛውን ፈጣን ሰዓት አስመዝግባለች፡፡
አትሌት ለተሰንበት ግደይ በበርሊን ኮንቲነንታል ቱር የሴቶች 5ሺህ ሜትር ሩጫ ፈጣን ሰዓት ሪከርድን ለመስበር ባትችልም 14 ደቂቃ ከ08 ሰከንድ በመግባት ነው 4ኛውን ፈጣን ሰዓቷን ያስመዘገበችው።
በሴቶች 5 ሺህ ሜትር ሩጫ አምስት…