ስፓርት
በ45ኛው የዓለም ሀገር አቋራጭ አትሌቲክስ ሻምፒዮና የሚሳተፈው ቡድን የማጠቃለያ ልምምድ አከናወነ
አዲስ አበባ፣ መጋቢት 14፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በሰርቢያ ቤልግሬድ በሚካሄደው 45ኛው የዓለም ሀገር አቋራጭ አትሌቲክስ ሻምፒዮና ኢትዮጵያን ወክሎ የሚሳተፈው ቡድን የማጠቃለያ ልምምዱን ዛሬ አከናወነ።
ከሳምንት በኋላ በፈረንጆቹ መጋቢት 30 ቀን 2024 በሚካሄደው ሻምፒዮና ላይ የሚሳተፈው የአትሌቲክስ ቡድን ጠንካራ ልምምድ ሲያካሂድ መቆየቱን የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን መረጃ አመልክቷል።
ቡድኑ ዛሬ የመጨረሻ ልምምዱን በኢትዮጵያ ስፖርት አካዳሚ ያካሄደ ሲሆን፤ በዚህም የትራክ ልምምድ በተጠናከረ መልኩ መስራቱ ተገልጿል።
Read More...
ኢትዮጵያ የመላ አፍሪካ የአትሌቲክስ ውድድርን ሁለተኛ ደረጃን በመያዝ አጠናቀቀች
አዲስ አበባ፣ መጋቢት 14፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ)ኢትዮጵያ የመላ አፍሪካ የአትሌቲክስ ውድድርን በ18 ሜዳሊያ ናይጄሪያን በመከተል በ2ኛ ደረጃን ይዛ አጠናቃለች፡፡
ላለፋት አምስት ቀናት በጋና አክራ ዩንቨርሲቲ ሲካሄድ የቆየው 13ኛው የመላ አፍሪካ የአትሌቲክስ ውድድር ተጠናቋል።
በውድድሩ ኢትዮጵያ በ47 ወንድ፣ በ40 ሴት በድምሩ…
ኢትዮጵያ በ1 ሺህ 500 ሜትር ሴቶች ሩጫ ውድድር የወርቅና የብር ሜዳሊያ አገኘች
አዲስ አበባ፣ መጋቢት 13፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በጋና እየተካሄደ ባለው 13ኛው የመላ አፍሪካ ጨዋታዎች ኢትዮጵያ በ1 ሺህ 500ሜትር ሴቶች ሩጫ ውድድር የወርቅና የብር ሜዳሊያ አገኘች።
በርቀቱ ለኢትዮጵያ የወርቅና የብር ሜዳሊያ ያመጡት አትሌት ሂሩት መሸሻ እና አትሌት ሀዊ አበራ ናቸው።
በውድድሩ አትሌት ሂሩት መሸሻ 4:05.71 በሆነ ሰዓት በማጠናቀቅ ውድድሩን…
ኢትዮጵያ በ5 ሺህ ሜትር ወንዶች ሩጫ ውድድር የወርቅ ሜዳሊያ አገኘች
አዲስ አበባ፣ መጋቢት 13፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በጋና እየተካሄደ ባለው 13ኛው የመላ አፍሪካ ጨዋታዎች ኢትዮጵያ በ5 ሺህ ሜትር ወንዶች ሩጫ ውድድር በሀጎስ ገብረህይወት አማካኝነት የወርቅ ሜዳሊያ አገኘች።
አትሌት ሀጎስ ገብረህይወት 13:38.12 በሆነ ሰዓት በማጠናቀቅ ውድድሩን በቀዳሚነት አሸንፏል።
ኢትዮጵያ በሴቶች የቦክስ ውድድር 2 የወርቅ ሜዳሊያ አገኘች
አዲስ አበባ፣ መጋቢት 13፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በጋና እየተካሄደ ባለው 13ኛው የመላ አፍሪካ ጨዋታዎች ኢትዮጵያ በ52 እና በ66 ኪሎ ግራም ሴቶች የቦክስ ውድድር 2 የወርቅ ሜዳሊያ አገኘች።
ቤተልሔም ገዛኸኝ ለሀገሯ የወርቅ ሜዳሊያ ያመጣችው በፍጻሜ ውድድሩ የሞሮኮዋን ቼዳል ራባብ 4ለ1 በሆነ ውጤት በማሸነፍ ነው።
በተመሳሳይ ኢትዮጵያዊቷ ቦክሰኛ…
አትሌት ዘውዲቱ አደራው በሴቶች ግማሽ ማራቶን የብር ሜዳሊያ አስገኘች
አዲስ አበባ፣ መጋቢት 13፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በ13ኛው የመላ አፍሪካ ጨዋታዎች የሴቶች ግማሽ ማራቶን ውድድር አትሌት ዘውዲቱ አደራው 2ኛ በመውጣት ለኢትዮጵያ የብር ሜዳሊያ አስገኝታለች፡፡
አሁን ላይ የወንዶቹ የ20 ኪሎ ሜትር ውድድር እየተካሄደ ሲሆን÷ አትሌት ተሰማ መኮነን፣ማስረሻ ብሪ እና ሃፍታሙ አባዲ ኢትዮጵያን ወክለዋል፡፡
ኢትዮጵያ በሴቶች 10 ሺህ ሜትር ሩጫ ውድድር ብርና ነሐስ አስመዘገበች
አዲስ አበባ፣ መጋቢት 12፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በ13ኛው የመላው አፍሪካ ጨዋታዎች ኢትዮጵያውያን አትሌቶች በሴቶች 10 ሺህ ሜትር ሩጫ ውድድር ብርና ነሐስ አስመዝግበዋል፡፡
በውድድሩ ውዴ ከፋለ ሁለተኛ የወጣች ሲሆን ፥ ተካን አማረ ሦስተኛ በመውጣት የብርና የነሐስ ሜዳሊያ ለሀገራቸው አስገኝተዋል፡፡