ስፓርት
የ2024 የፓሪስ ኦሎምፒክ የችቦ ማብራት ፕሮግራም በቦንጋ ከተማ እየተካሄደ ነው
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 3፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) "ኢትዮጵያ ትወዳዳር፣ ተወዳድራም ታሸንፍ'' በሚል መሪ ሀሳብ የ2024 የፓሪስ ኦሎምፒክ የችቦ ማብራት ፕሮግራም በቦንጋ ከተማ እየተካሄደ ይገኛል።
በስነ ስርዓቱ ላይ የኢትዮጵያ ኦሎምፒክ ኮሚቴ ፕሬዚዳንት አሸብር ወልደጊዮርጊስ (ዶ/ር)፣ የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ፕሬዚዳንት ረዳት ኮሚሽነር ደራርቱ ቱሉ እና የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ከፍተኛ ሀላፊዎች ተገኝተዋል፡፡
የፓሪስ ኦሎምፒክ የችቦ ማብራት ፕሮግራም ቀደም ሲል በመቀሌ፣ በደሴ፣ በሰመራ እና በቢሾፍቱ ከተሞች መካሄዱ…
Read More...
ኪሊያን ምባፔ በውድድር ዓመቱ መጨረሻ ከፒኤስጂ ጋር እንደሚለያይ ይፋ አደረገ
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 2፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) ኪሊያን ምባፔ በውድድር ዓመቱ መጨረሻ ከፒኤስጂ ጋር እንደሚለያይ ይፋ አድርጓል፡፡
ፈረንሳያዊው አጥቂ ምባፔ ሪያል ማድሪድን ይቀላቀላል ተብሎ ይጠበቃል፡፡
በዶሃ የዳይመንድ ሊግ 3 ሺህ መሰናክል የሩጫ ውድድር አትሌት ሳሙኤል ፍሬው በቀዳሚነት አጠናቀቀ
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 2፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በኳታር ዶሃ በተካሄደ የዳይመንድ ሊግ 3 ሺህ መሰናክል የሩጫ ውድድር አትሌት ሳሙኤል ፍሬው በቀዳሚነት አጠናቀቀ።
አትሌቱ ውድድሩን 8:07.25 በሆነ ጊዜ በመግባት ነው ውድድሩን ያሸነፈ ሲሆን፤ ኬንያዊው አትሌት ኪበብዎት አብራሃም 8:07.38 እንዲሁም አትሌት ጌትነት ዋለ 8:09.69 በሆነ ጊዜ በመግባት ሁለተኛ እና ሶስተኛ…
በዶሃ በተካሄደ የዳይመንድ ሊግ የሩጫ ውድድር አትሌት ፍሬወይኒ ሀይሉ በቀዳሚነት አጠናቀቀች
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 2፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በኳታር ዶሃ በተካሄደ የዳይመንድ ሊግ 1 ሺህ 500 ሜትር የሩጫ ውድድር ፍሬወይኒ ሀይሉ በቀዳሚነት አጠናቀቀች፡፡
አትሌቷ ውድድሩን 4:00.42 በሆነ ጊዜ በመግባት ነው ያሸነፈችው።
ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ወልቂጤ ከተማን በማሸነፍ መሪነቱን አጠናከረ
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 2፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 24ኛ ሳምንት የሊጉ መሪ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ወልቂጤ ከተማን በማሸነፍ መሪነቱን አጠናከረ።
ምሽት 12:00 ሰዓት ላይ በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ወልቂጤ ከተማን 2 ለ 1 በሆነ ውጤት አሸንፏል።
ለኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ሱሌማን ሀሚድ እና ፉዓድ ፈረጃ…
ኢትዮጵያ መድን ቅዱስ ጊዮርጊስን አሸነፈ
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 2፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 24ኛ ሳምንት ኢትዮጵያ መድን ቅዱስ ጊዮርጊስን 1 ለ 0 በሆነ ውጤት አሸነፈ።
ዛሬ ቀን 9 ሰዓት ላይ በተካሄደ የሊጉ ጨዋታ ኢትዮጵያ መድን ብሩክ ሙሉጌታ ባስቆጠራት ግብ ሶስት ነጥብ ይዞ ወጥቷል።
ፋሲል ከነማ እና ባህርዳር ከተማ አቻ ተለያዩ
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 1፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) ፋሲል ከነማ እና ባህርዳር ከተማን ያገናኛኘው የወንድማማቾች ደርቢ ባዶ ለባዶ በሆነ አቻ ውጤት ተጠናቀቀ፡፡
ቀን 9 ሰዓት ላይ በተደረገው የ24ኛ ሳምንት የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ መርሃ ግብር ተመጣጣኝ የጨዋታ እንቅስቃሴን አስተናግዷል።
ክለቦቹ በሊጉ 10 ጊዜ የተገናኙ ሲሆን የዛሬውን ጨዋታ ጨምሮ 7 ጊዜ በአቻ ውጤት…