Fana: At a Speed of Life!

ስፓርት

በፕሪሚየር ሊጉ መቻል ድል ቀንቶታል

አዲስ አበባ፣ ታህሳስ 10፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በቤትኪንግ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ መቻል ባህርዳር ከነማን 3 ለ 2 በሆነ ውጤት አሸንፏል፡፡ በድሬዳዋ ስታዲየም ቀን 10 ሰዓት በተደረገው ጨዋታ መቻል ከመመራት ተነስቶ በሃሉ ግርማ፣ በረከት ደስታ እና ከነዓን ማርክነህ ባስቆጠሯቸው ግቦችአሸናፊ መሆን ችሏል፡፡ ውጤቱን ተከትሎ የጣና ሞገዶቹ ፕሪሚየር ሊጉን የሚመሩበትን እድል ሲያመክኑ÷ መቻል በአንፃሩ አራት ደረጃዎችን በማሻሻል ከወልቂጤ ከነማ ጋር እኩል 7ኛ ደረጃ ላይ መቀመጥ ችሏል፡፡ የ13ኛ ሳምንት ጨዋታዎች በድሬዳዋ ስታዲየም…
Read More...

በዓለም ዙሪያ ያሉ የፈረንሳይ ደጋፊዎችን በማስደሰታችሁ ኮርተንባችኋል – ኢማኑኤል ማክሩን ለብሄራዊ ቡድናቸው

አዲስ አበባ፣ ታኅሣሥ 10፣ 2015 (ኤፍ ቢሲ) በዓለም ዙሪያ ያሉ የፈረንሳይ ደጋፊዎችን በማስደሰታችሁ ኮርተንባችኋል ሲሉ የፈረንሳዩ ፕሬዚዳንት ኢማኑኤል ማክሮን ለሀገራቸው ብሄራዊ ቡድን ተናግረዋል፡፡ ፕሬዚዳንቱ በፍፃሜ ጨዋታው በአርጅንቲና በመለያ ምት ተሸንፎ ዋንጫውን ያጣውን ብሄራዊ ቡድናቸውን መልበሻ ክፍል ድረስ በመሄድ አፅናንተዋል፡፡ በማህበራዊ ሚዲያዎች…

የፕሪሚየር ሊጉ የዲ ኤስ ቲቪ የቀጥታ ስርጭት ሽፋን ዛሬ በሚደረጉ ጨዋታዎች ይጀመራል

አዲስ አበባ፣ ታኅሣሥ 10፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 13ኛ ሳምንት መርሐግብር ዛሬ በሚካሄዱ ሁለት ጨዋታዎች ይጀመራል። በዓለም ዋንጫው ምክንያት ተቋርጦ የነበረው የፕሪሚየር ሊጉ ጨዋታዎች የዲ ኤስ ቲቪ የቀጥታ ስርጭት እንደሚጀመርም ተገልጿል። ባህር ዳር ከተማ ከመቻል ከቀኑ 10 ሰአት እንዲሁም ኢትዮ ኤሌክትሪክ ከሀድያ ሆሳዕና ከምሽቱ…

አርጀንቲና የኳታሩ ዓለም ዋንጫ ሻምፒዮን ሆነች

አዲስ አበባ፣ ታኅሣሥ 9፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) አርጀንቲና ፈረንሳይን በመለያ ምት በማሸነፍ የኳታሩ ዓለም ዋንጫ ሻምፒዮን ሆናለች፡፡   የ22ኛው የኳታር ዓለም ዋንጫ የፍጻሜ ጨዋታ ምሽት 12 ሰዓት ላይ በሉሳይል አይኮኒክ ስታዲየም ተካሂዷል፡፡   በዚህም ፈረንሳይ እና አርጀንቲና መደበኛ ጨዋታውን 2 ለ 2 በሆነ አቻ ውጤት ያጠናቀቁ ሲሆን÷…

የዓለም ዋንጫ የፍጻሜ ጨዋታ ዛሬ ይካሄዳል

አዲስ አበባ፣ ታኅሣሥ 9፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ)የ22ኛው የኳታር ዓለም ዋንጫ የፍጻሜ ጨዋታ በአርጀንቲና እና በፈረንሳይ መካከል ዛሬ ይካሄዳል፡፡ በፈረንጆቹ አቆጣጠር ህዳር 20 በኳታር መካሄድ የጀመረው የዓለም ዋንጫ ጨዋታ ዛሬ ፍፃሜውን ያደርጋል፡፡ በዓለም ዋንጫው 32 ሀገራት ተሳትፈዋል፤ሴኔጋል ፣ጋና፣ ካሜሮን፣ ቱኒዚያና ሞሮኮ ደግሞ አፍሪካን የወከሉ ሀገራት ሲሆኑ÷…

ክሮሽያ በአለም ዋንጫ 3ኛ ደረጃን ይዛ አጠናቀቀች

በአዲስ አበባ፣ ታኅሣሥ 8፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በኳታር የዓለም ዋንጫ ክሮሽያ ሞሮኮን 2 ለ 1 በማሸነፍ 3ኛ ደረጃን ይዛ አጠናቃለች፡፡ ጨዋታው ዛሬ ምሽት 12 ሰዓት ላይ የተደረገ ሲሆን÷በ2022ቱ የዓለም ዋንጫ ሞሮኮ ከክሮሽያ ጋር ያደረገችው ጨዋታ በዘንድሮው የዓለም ዋንጫ 3ኛ ሆኖ የሚያጠናቅቀው ብሔራዊ ቡድን የተለየበት ነው፡፡ ሞሮኮ 3ኛ ደረጃን ይዛ የማጠናቀቅ…

የቀድሞው የዩጎዝላቪያ ተጫዋች ሲንሳ ሚሃይሎቪች ከዚህ ዓለም በሞት ተለየ

አዲስ አበባ ፣ ታኅሣሥ 7 ፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የቀድሞው የኢንተር ሚላን እና ላዚዮ ተከላካይ ሲንሳ ሚሃይሎቪች ከዚህ ዓለም በሞት ተለየ። ሚሃይሎቪች በዛሬው እለት በጣሊያን ሮም ህይወቱ ማለፉን ደይሊ ሜይል አስነብቧል። በድንቅ ቅጣት ምት ጎሎቹ የሚታወቀው የቀድሞዋ ዩጎዝላቪያ ጠንካራ ቡድን አባል የነበረው ሚሃይሎቪች በ53 አመቱ ነው ከዚህ ዓለም በሞት የተለየው።…