Fana: At a Speed of Life!

ስፓርት

የቻይና ቤጂንግ የበጋ ኦሎምፒክ ውድድሮች ዓለምአቀፋዊ አንድነትን እና ትብብርን አጠናክረዋል – ሺ ጂንፒንግ

አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 1፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) ቻይና አለመረጋጋቶች በሰፈኑበት ወቅት የቤጂንጉን የኦሎምፒክ እና ፓራ-ኦሎምፒክ ውድድሮች በብቃት ማስተናገድ መቻሏ በራስ መተማመንን፣ ተሥፋን እና አንድነትን ለዓለም ያመጣ ክስተት መሆኑን የቻይናው ፕሬዚዳንት ሺ ጂንፒንግ ገለጹ፡፡ ሺ ጂንፒንግ ÷ በትናንቱ ጉባዔ ለኦሎምፒኮቹ መሳካት የላቀ አስተዋፅኦ ላበረከቱ አካላት ሽልማት ሰጥተዋል፡፡ ሽልማቶቹ የተሰጡትም በጨዋታዎቹ በ148 ስምሪቶች ውስጥ ከፍተኛ ሚና ለነበራቸው አካላት እና በጨዋታው የላቀ አስተዋፅኦ ላበረከቱ 148 ግለሰቦች መሆኑ…
Read More...

ፋሲል ከነማ ከአሠልጣኙ ስዩም ከበደ ጋር በሥምምነት ተለያየ

አዲስ አበባ፤ ሚያዚያ 1፣2014(ኤፍ ቢ ሲ) የአምናው ሻምፒዮን ፋሲል ከነማ ከአሠልጣኙ ስዩም ከበደ ጋር በሥምምነት ተለያይቷል። ያለፉትን ሁለት ዓመታት ከመንፈቅ አፄዎቹን በዋና አሠልጣኝነት የመሩት ስዩም ከበደ ክለቡ በታሪኩ ለመጀመሪያ ጊዜ ዋንጫ እንዲያነሳ ማድረጋቸው ይታወሳል፡፡ ይሁን እንጅ ቡድኑ በዘንድሮው የውድድር ዓመት የውጤት ቀውስ ውስጥ መግባቱን ተከትሎ…

የቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል በእግር ኳስ ውጤታማ እንዲሆን ድጋፍ ይደረጋል – የእግር ኳስ ፌዴሬሽን

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 30፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል በእግር ኳስ ስፖርት ውጤታማ እንዲሆን አስፈላጊውን ድጋፍ እንደሚያደርግ የኢትዮጵያ እግርኳስ ፌዴሬሽን አስታወቀ። በፌዴሬሽኑ ፕሬዚዳንት አቶ ኢሳያስ ጅራ የተመራ ልዑክ በአሶሳ ከተማ ከ15 ዓመት በታች ለሚገኙ ፓይለት ፕሮጀክት የኳስ እና ኮን ድጋፍ አድርጓል። በድጋፍ ርክክቡ ወቅት…

የኢትዮጵያ የማራቶን ዱላ ቅብብል ውድድር በሶማሌ ክልል ይካሄዳል

አዲስ አበባ፣መጋቢት 30፣ 2014(ኤፍ ቢ ሲ) 17ኛው የኢትዮጵያ የማራቶን ዱላ ቅብብል ውድድር ሚያዚያ 9 ቀን 2014 ዓ.ም በሶማሌ ክልል ጅግጅጋ ከተማ ይካሄዳል። በውድድሩ ላይ ክልሎች፣ ከተማ አስተዳደሮች፣ ክለቦች፣ የአትሌቲክስ ማሰልጠኛ ማዕከላትና ተቋማት እንደሚሳተፉ የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን አስታውቋል። የውድድሩ አላማ ለክልሎች፣ ከተማ…

አራት ኢትዮጵያዊ እንስት ዳኞች የዓለም ከ17 ዓመት በታች ዋንጫ ማጣሪያ ጨዋታን ይመራሉ

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 29፣ 2014 (ኤፍ ቢሲ) አራት ኢትዮጵያዊ እንስት ዳኞች የዓለም ከ17 ዓመት በታች ዋንጫ ማጣሪያን ጨዋታን እንደሚመሩ ካፍ አስታወቀ፡፡ በህንድ አስተናጋጅነት ለሚካሄደው የዓለም ከ17 ዓመት በታች ሴቶች የዓለም ዋንጫ ማጣሪያ ውድድር ላይ ለመካፈል ኢትዮጵያን ጨምሮ የተለያዩ ሀገራት የማጣሪያ ጨዋታዎችን እያደረጉ ይገኛሉ፡፡ በማጣሪያው ኢትዮጵያ…

ወጋየሁ በኃይሉ – የኢንተርናሽናል ቴኳንዶ የማስተር የአሠልጣኝነት ደረጃ ያገኘ የመጀመሪያው ኢትዮጵያዊ ሆነ

አዲስ አበባ ፣ መጋቢት 28 ፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) ወጋየሁ በኃይሉ የኢንተርናሽናል ቴኳንዶ የማስተር የአሰልጣኝነት ደረጃን ያገኙ የመጀመሪያው ኢትዮጵያዊ  ሆነዋል። የኢንተርናሽናል ኢንስትራክተር ማዕረግ የነበራቸው ወጋየሁ በኃይሉ ÷ ትናንት የነበራቸውን የተግባር ፈተና በብቃት በመወጣት ወደ ማስተር (ደረጃ ሰባት) ከፍ ማድረጋቸውን ተናግረዋል። አሰልጣኙን በተግባር…

ኢትዮጵያ ከ17 አመት በታች የሴካፋ ዋንጫ ማጣሪያ ውድድርን ታስተናግዳለች

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 28፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) ኢትዮጵያ በሴካፋ ስር ከሚደረጉ ውድድሮች አንዱ የሆነውን ከ17 አመት በታች የምስራቅ እና መካከለኛው የአፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያ ውድድርን ታስተናግዳለች፡፡ በምስራቅና መካከለኛው አፍሪካ ብሄራዊ ፌዴሬሽኖች የተዋቀረው ሴካፋ በስሩ የሚደረጉ 7 ወድድሮችን የሚያስተናግዱ ሀገራት ዝርዝር ይፋ አድርጓል። የሴካፋ ዋና ዳይሬክተር…