ስፓርት
በቤትኪንግ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ኢትዮጵያ ቡና ድል ቀንቶታል
አዲስ አበባ፣ግንቦት 13፣2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በ24ኛ ሳምንት የቤትኪንግ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ኢትዮጵያ ቡና ድል ቀንቶታል፡፡
ከሀዋሳ ከተማ ጋር የተጫወተው ኢትዮጵያ ቡና 3 ለ 1 በሆነ ውጤት ማሸነፍ ችሏል፡፡
የኢትዮጵያ ቡናን የድል ጎሎች አላዛር ሽመልስ እና አማኑኤል ዮሃንስ እንዲሁም ዳግም ተፈራ በራሱ መረብ ላይ ሲያስቆጥር ብሩክ በየነ የሀዋሳ ከተማን ብቸኛ ጎል አስቆጥሯል፡፡
ኢትዮጵያ ቡና ዛሬ ማሸነፉን ተከትሎ በእኩል 37 ነጥብ ከሲዳማ ቡና ጋር 3ኛ ደረጃ ላይ መቀመጥ ችሏል፡፡
ረፋድ ላይ በተደረገ ሌላ መርሃ ግብር አዲስ…
Read More...
የኢትዮጵያ ከ17 ዓመት በታች የሴቶች ብሄራዊ ቡድን በናይጄሪያ አቻው ተሸነፈ
አዲስ አበባ፣ግንቦት 12፣2014 (ኤፍ ቢሲ) የኢትዮጵያ ከ17 ዓመት በታች የሴቶች ብሄራዊ ቡድን በናይጄሪያ አቻው 1ለ 0 ተሸንፏል፡፡
ዛሬ ቡድኑ የዓለም ዋንጫ ማጣርያ የመጨረሻ ዙር የመጀመርያ ጨዋታውን በአበበ ቢቂላ ስታዲየም ከናይጄሪያ አቻው ጋር አድርጓል፡፡
በጫዎታውም የኢትዮጵያ ከ17 ዓመት በታች የሴቶች ብሄራዊ ቡድን በናይጄሪ አቻው 1ለ 0 ተሸንፏል፡፡
የኢትዮጵያ ወንዶች ብሔራዊ ቡድን ለ28 ተጫዋቾች ጥሪ አቀረበ
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 12፣ 2014 (ኤፍ ቢሲ) የኢትዮጵያ ወንዶች ብሔራዊ ቡድን በአፍሪካ ዋንጫ ማጣርያ ከማላዊ እና ግብፅ ጋር ለሚያደርጋቸው ጨዋታዎች ዝግጅት ለ28 ተጫዋቾች ጥሪ አቀረበ፡፡
በአሰልጣኝ ውበቱ አባተ የሚመሩት ዋልያዎቹ በግንቦት 25 እና 29 ከማላዊ እና ግብጽ ብሄራዊ ቡድኖች ጋር የ2023 አፍሪካ ዋንጫ የምድብ ማጣሪያ ጨዋታ በማላዊ ዋና…
በሦስት የእግር ኳስ ዳኞች ላይ የቅጣት ውሳኔ ተላፈ
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 12፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በወላይታ ዲቻ እና በኢትዮጵያ ቡና የእግር ኳስ ቡድኖች ክስ የተመሰረተባቸው ሦስት የእግር ኳስ ዳኞች ላይ የቅጣት ውሳኔ ተላለፈ፡፡
በኢትዮጵያ ቤትኪንግ ፕሪሚየር ሊግ የ24ኛ ሣምንት ጨዋታ የኢትዮጵያ ቡና ከሀድያ ሆሳዕና ያደረጉትን ጨዋታ በዋና ዳኝነት የመሩት ፌደራል ዳኛ ሚካኤል ጣዕመ በተጫዋቾች…
ቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የ2015ቱ ውድድር መስከረም 20 ቀን ይጀመራል
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 10፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) ቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የ2015ቱ ውድድር የፊታችን መስከረም 20 ቀን እንደሚጀመር የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ አክሲዮን ማህበር አስታውቋል፡፡
የክረምቱ የዝውውር መስኮትም የፊታችን ሐምሌ 1 ቀን 2014 ዓ.ም እንደሚከፈት ሶከር ኢትዮጵያ ዘግቧል፡፡
ቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ…
በፕሪሚየር ሊጉ ፋሲል ከነማ እና ሰበታ ከተማ ድል ቀንቷቸዋል
አዲስ አበባ፣ግንቦት 10፣2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በቤትኪንግ ኢትዮጵያ ፐሪሚየርሊግ ፋሲል ከነማ መከላከያን 2 ለ 1 አሸንፏል፡፡
ሽመክት ጉግሳ እና ናትናኤል ገብረ ጊዮርጊስ የፋሲል ከነማን የድል ጎሎች ሲያስቆጥሩ አሚን ነስሩ ብቸኛዋን የመከላከያ ጎል አስቆጥሯል፡፡
ውጤቱን ተከትሎም ፋሲል ከነማ ደረጃውን ሲያስጠብቅ መከላከያ በነበረበት 8ኛ ደረጃ ላይ…
አዳማ ከተማ ከአሰልጣኝ ፋሲል ተካልኝ ጋር በስምምነት ተለያየ
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 10፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) ያለፉትን አስር ጨዋታዎች በሊጉ ማሸነፍ ያልቻለው አዳማ ከተማ ከአሰልጣኝ ፋሲል ተካልኝ ጋር በስምምነት ተለያየ፡፡
የዘንድሮ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ከመጀመሩ በፊት አዳማ ከተማን ለማሰልጠን ፊርማውን ያኖረው አሠልጣኝ ፋሲል ተካልኝ÷ በዝውውር መስኮቱ ራሱን በማጠናከር ውድድር ቢጀምርም እስካሁን ከአራት…