ስፓርት
የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን ለመጀመሪያ ጨዋታ ልምምዱን አጠናክሮ ቀጥሏል
አዲስ አበባ፣ታህሳስ 29፣2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን እሁድ ምሽት አራት ሰዓት ላይ ከኬፕ ቨርዴ ጋር ለሚያደርገው የአፍሪካ ዋንጫ የመጀመርያ ጨዋታ ልምምዱን በተጠናከረ ሁኔታ ማከናወኑን ቀጥሏል።
በዛሬው የልምምድ መርሐ ግብር ላይም የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ዋና ፀሐፊ አቶ ባሕሩ ጥላሁን ተገኝተው ቡድኑን መመልከታቸውን ከፌደሬሽኑ ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡
ኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድኑ ቀደም ሲል በካሜሮን ዋና ከተማ አኔክስ 2 በተባለው የልምምድ ሜዳ ልምምድ ሲያደርጉ መቆየቱ የሚታወስ ነው ።
Read More...
በጣሊያን በተካሄደ አገር አቋራጭ ውድድር ኢትዮጵያውያን አትሌቶች አሸነፉ
አዲስ አበባ፣ ታህሳስ 29፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የዓለም አትሌቲክስ ቱር አካል በሆነውና በጣሊያን በተደረገው አገር አቋራጭ የአትሌቲክስ ውድድር አትሌት ዳዊት ስዩምና ይሁኔ አዲሱ በሁለቱም ፆታዎች አንደኛ በመውጣት አሸንፈዋል፡፡
በወንዶች 10 ኪሎ ሜትር ይሁኔ አዲሱ በ28 ደቂቃ ከ39 ሰከንድ 1ኛ ደረጃን ይዟል፡፡
በሴቶች 6 ኪሎ ሜትር ዳዊት ስዩም በ18 ደቂቃ…
12ኛው የአዲስ አበባ ከተማ የባህል ስፖርት ፌስቲቫል መካሄድ ጀመረ
አዲስ አበባ፣ ታህሳስ 27፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ)12ኛው የአዲስ አበባ ከተማ የባህል ስፖርት ፌስቲቫል በጃን ሜዳ መካሄድ ጀምሯል።
በመርሃ ግብሩ መክፈቻ ላይ ንግግር ያደረጉት የአዲስ አበባ ባህል ኪነጥብና ቱሪዝም ቢሮ ኃላፊ ዶክተር ሂሩት ካሳው፤ የባህል ስፖርቶች ለዘመናዊ ስፖርት መሰረት በመሆናቸው ማሳደግ ያስፈልጋል ብለዋል።
የባህል ስፖርቶችን በማሳደግ ዘርፈ ብዙ…
የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ጉባኤ የተለያዩ ውሳኔዎችን በማሳለፍ ተጠናቀቀ
አዲስ አበባ፣ ታህሳስ 24፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን 13ኛ መደበኛ ጠቅላላ ጉባኤ የተለያዩ ውሳኔዎችን በማሳለፍ ተጠናቋል፡፡
ከዚህ ቀደም በተፈጠረው የአሰራር ክፍተት ምክንያት ከኢትዮጵያ አግር ኳስ ፌዴሬሽን የስራ አስፈፃሚነት ታግደው የቆዩት ወይዘሮ ሶፍያ አልማሙን ወደ ስራ አስፈፃሚነት ቦታቸው እንዲመለሱ የውሳኔ ሀሳብ ለጉባኤተኛው ቀርቦ በሙሉ…
የዓለም የ5 ኪሎ ሜትር የጎዳና ሩጫ ውድድርን ኢትዮጵያውያን አትሌቶች በሁለቱም ጾታ ሪከርድ በመስበር አሸነፉ
አዲስ አበባ፣ ታህሳስ 23፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የዓለም የ5 ኪሎ ሜትር የጎዳና ላይ ሩጫ ውድድርን በሪሁ አረጋዊና እጅጋየሁ ታዬ ሪከርድ በመስበር ጭምር አሸነፉ፡፡
በፈረንጆቹ የ2021 የመጨረሻዋ ቀን በስፔን ባርሴሎና በተደረገ የ5 ኪሎ ሜትር የጎዳና ላይ ሩጫ ውድድር በሁለቱም ፆታ ኢትዮጵያውያኑ ሪከርድ ሰብረው ማሸነፋቸውን ከአትሌቲክስ ፌዴሬሽን…