Fana: At a Speed of Life!

ስፓርት

በቤትኪንግ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ሃድያ ሆሳዕና ድል ቀንቶታል

በአዲስ አበባ፣ሚያዝያ 11፣2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በ19ኛ ሳምንት የቤትኪንግ ኢትዮጵያ ፕርሚየር ሊግ ሀድያ ሆሳዕና አዳማ ከተማን 2 ለ 1 አሸንፏል፡፡ ሀድያ ሆሳዕና ኦሞድ ኡኩሪ ከረጅም ጊዜ በኋላ ባስቆጠራት ጎል እስከ ዕረፍት 1 ለ 0 መምራት ችሏል፡፡ ከዕረፍት መልስ አዳማ ከተማ በአሜ ሙሀመድ ጎል አቻ መሆን ቢችልም ራምኬ ሎክ በ 87ኛው ደቂቃ ባስቆጠራት ጎል ነብሮቹ ወሳኝ 3 ነጥብ ማግኘት ችለዋል፡፡ ሀድያ ሆሳዕና ዛሬ ማሸነፉን ተከትሎ በ 25 ነጥብ 4 ደረጃዎችን በማሻሻል ለጊዜው 7ኛ ደረጃ ላይ መቀመጥ ችሏል፡፡…
Read More...

በፕሪምየርሊጉ ድሬዳዋ ከተማ ደረጃውን ያሻሻለበትን ውጤት አስመዘገበ

አዲስ አበባ፣ሚያዚያ 10፣2014 (ኤፍ ቢሲ) በ19ኛ ሳምንት የቤትኪንግ ኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ ድሬዳዋ ከተማ ጅማ አባ ጅፋርን 2 ለ 1 በማሸነፍ ደረጃውን አሻሸሏል፡፡ ከደቂቃዎች በፊት በተካሄደው ጨዋታ አንጋፋው ተጫዋች ጋዲሳ መብራቴ እና ሄኖክ አየለ የድሬዳዋን የአሸናፊነት ጎል ሲያሰቆጥሩ ዳዊት በፍቃዱ ብቸኛዋን የጅማ አባ ጅፋር ጎል አስቆጥሯል፡፡ የጨዋታውን…

የታዳጊዎች የፓይለት ፕሮጀክቶችን ፍሬ የምናይበት ጊዜ ሩቅ አይሆንም -አቶ ኢሳያስ ጅራ

አዲስ አበባ፣ሚያዚያ 10፣2014 (ኤፍ ቢሲ) በየክልሉ የሚገኙ የታዳጊዎች የፓይለት ፕሮጀክቶችን ፍሬ የምናይበት ጊዜ ሩቅ አይደለም ሲሉ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ፕሬዚደንት አቶ ኢሳያስ ጅራ ተናገሩ፡፡ ፕሬዚደንቱ ከሰሞኑ በተለያዩ ክልሎች የሚካሄዱትን የታዳጊዎች እግር ኳስ ፓይለት ፕሮጅክቶች ከጎበኙ በኋላ ከፌዴሬሽኑ የዝግጅት ክፍል ጋር ቆይታ ባደረጉት ቆይታ…

በሐዋሳ ከተማ ሲካሄድ የቆየው 4ኛው የመላ ኢትዮጵያ ሴቶች ጨዋታ ተጠናቀቀ

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 10፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በባህልና ስፖርት ሚኒስቴር አዘጋጅነት ከሚያዝያ 1 እስከ 9 ቀን 2014 ዓ.ም "የሴቶች እኩል ተሳታፊነት ለስፖርት ውጤታማነት" በሚል መሪ ቃል ለአንድ ሳምንት ሲካሄድ የቆየው 4ኛው የመላ ሴቶች ጨዋታ ተጠናቋል። ኦሮሚያን ከሲዳማ ባገናኘው የፍጻሜ የእግር ኳስ ጨዋታ ኦሮሚያ 3 ለ 1 በሆነ ውጤት አሸናፊ…

በፕሪሚየርሊጉ ሳላዲን ሐት ትሪክ ሲሰራ ቅዱስ ጊዮርጊስ አቻ ተለያይቷል

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 9፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ዛሬ ሁለት ጨዋታዎች ተደርገዋል። ቀደም ብሎ በተካሄደ ጨዋታ መሪው ቅዱስ ጊዮርጊስ ከመከላከያ ያለምንም ጎል አቻ ተለያይቷል። ማምሻውን በተካሄደ ጨዋታ ደግሞ ሰበታ ከተማ ከሲዳማ ቡና ተገናኝተዋል። ጨዋታው በሲዳማ ቡና 3 ለ 0 አሸናፊነት ሲጠናቀቅ…

17ኛው የኢትዮጵያ ማራቶን ሪሌ ውድድር በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ቡድን የበላይነት ተጠናቀቀ

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 9፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) 17ኛው የኢትዮጵያ ማራቶን ሪሌ ውድድር በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ቡድን የበላይነት ተጠናቀቀ፡፡ በጂግጂጋ ከተማ ሲካሄድ የቆየው 17ኛው የኢትዮጵያ ማራቶን ሪሌ ውድድር ፍፃሜውን አግኝቷል። በውድድሩ÷ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ቡድን አንደኛ በመውጣት የዋንጫ ተሸላሚ ሲሆን÷ ኢትዮ ኤሌክትሪክ ሁለተኛ…

የ2022 ካዛኪስታን – ዱሻንቤ ኢንተርናሽናል ግማሽ ማራቶን ውድድር ኢትዮጵያውያን አትሌቶች ድል ቀናቸው

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 9፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የ2022 ካዛኪስታን - ዱሻንቤ ኢንተርናሽናል ግማሽ ማራቶን ውድድር ኢትዮጵያውያን አትሌቶች ድል ቀንቷቸዋል፡፡ በሴቶች አትሌት በቀሉ አበበ የ2022 ካዛኪስታን - ዱሻንቤ ኢንተርናሽናል ግማሽ ማራቶን ውድድር አሸናፊ ሆናለች፡፡ በተመሳሳይ መርሐ ግብር በወንዶች አትሌት ግርማ ጥላሁን ሁለተኛ ደረጃን…