ስፓርት
በቻምፒየንስ ሊጉ ሪያል ማድሪድ እና ማንቼስተር ሲቲ ድል ቀንቷቸዋል
አዲስ አበባ፣ የካቲት 18፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) የአውሮፓ ቻምፒየንስ ሊግ የጥሎ ማለፍ ጨዋታዎች ትናንት ምሽት ተደርገዋል፡፡
በምሽቱ በተደረጉ ሁለት ጨዋታዎች ሪያል ማድሪድ እና ማንቼስተር ሲቲ ድል ቀንቷቸዋል፡፡
አታላንታ በሪያልማድሪድ 1 ለ 0 ሲሸነፍ፥ ፈርላንድ ሜንዲ ለሪያል ማድሪድ የመጀመሪያውን የቻምፒየንስ ሊግ ጎሉን አስቆጥሯል፡፡
ቦሩሲያ ሞንቼግላድባህ ከማንቼስተር ሲቲ ባደረጉት ጨዋታ ደግሞ ማንቼስተር ሲቲ 2 ለ 0 በሆነ ውጤት አሸንፏል፡፡
በርናንዶ ሲልቫ እና ጋብሬል የሱስ የድል ጎሎቹን ለእንግሊዙ ክለብ አስቆጥረዋል፡፡…
Read More...
በማድሪድ የቤት ውስጥ የሩጫ ውድድር ኢትዮጵያውያን አትሌቶች ድል ቀንቷቸዋል
አዲስ አበባ ፣ የካቲት 18 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) በስፔን ማድሪድ በተካሄደ የቤት ውስጥ የአትሌቲክስ ውድድር ኢትዮጵያውያን አትሌቶች ድል ቀንቷቸዋል፡፡
በሴቶች የ3 ሺህ ሜትር አትሌት ጉዳፍ ፀጋይ 8 ደቂቃ ከ22 ሰከንድ ከ65 ማይክሮ ሰከንድ በሆነ ጊዜ በመግባት አሸናፊ ሆናለች፡፡
ሌላዋ ኢትዮጵያዊት አትሌት ለምለም ሃይሉ እና ኬንያዊቷ ቢትሪስ ቺቤት 2ኛ እና 3ኛ…
ፋሲል ከነማ ከሰበታ ከተማ ጋር አቻ ተለያየ
አዲስ አበባ፣ የካቲት 17፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) በ12ኛው ሳምንት የቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ፋሲል ከነማና ሰበታ ከተማ አንድ አቻ ተለያዩ፡፡
ለፋሲል ከነማ ሽመክት ጉግሳ በአምስተኛው ደቂቃ ሲያስቆጥር ቡልቻ ሱራ ለሰበታ ከተማ በ77 ደቂቃ ላይ አስቆጥሯል፡፡
ረፋድ ቀደም ብሎ በተካሄደው ጨዋታ ሀዲያ ሆሳዕና ጅማ አባ ጅፋርን 1 ለ 0 አሸንፏል፡፡
ፋሲል…
ሀዲያ ሆሳዕና ጅማ አባ ጅፋርን አሸነፈ
አዲስ አበባ፣ የካቲት 17፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) በ12ኛው ሳምንት የቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ሀዲያ ሆሳዕና ጅማ አባ ጅፋርን 1 ለ 0 አሸነፈ፡፡
የሀዲያ ሆሳዕናን የማሸነፊያ ብቸኛ ግብ በመጨረሻዎቹ ደቂቃዎች ካሉሻ አልሃሰን አስቆጥሯል፡፡
የሊጉ መሪ ፋሲል ከነማና ሰበታ ከተማ ጨዋታቸውን ከሰዓት በባህርዳር ስታዲየም ያካሄዳሉ፡፡
ሊጉን ፋሲል ከነማ በ28…
ቅዱስ ጊዮርጊስ ወልቂጤ ከተማን አሸነፈ
አዲስ አበባ ፣ የካቲት 16፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) በ12ኛው ሳምንት የቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ቅዱስ ጊዮርጊስ ወልቂጤ ከተማን 4 ለ 3 አሸነፈ፡፡
ሁለቱ ቡድኖች ጨዋታቸውን በ9፡00 ሰዓት በባህርዳር ስታዲየም አካሂደዋል፡፡
የቅዱስ ጊዮርጊስን ሁለት ግቦች ጌታነህ ከበደ ሲያስቆጥር ቀሪዎቹን አቤል እንዳለ እና አብዱልከሪም መሐመድ አስቆጥረዋል፡፡
ሊጉን ፋሲል ከነማ…
የኢትዮጵያ ባህል ስፖርቶች ውድድር ከእሁድ ጀምሮ በድሬዳዋ ይካሄዳል
አዲስ አበባ፣ የካቲት 16፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) 18ኛው የኢትዮጵያ ባህል ስፖርቶች ውድድር እና 14ኛው የኢትዮጵያ ባህል ስፖርቶች ፌስቲቫል ከየካቲት 21 እስከ 27 ዓ.ም በድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር ይካሄዳል፡፡
የኢትዮጵያ ባህል ስፖርቶች ፌዴሬሽን ፕሬዚዳንት አቶ ሰለሞን አስፋው ከትግራይ ክልል በስተቀር ሁሉም ክልሎችና ከተማ አስተዳደሮች እንደሚሳተፉ ገልጸዋል፡፡…
የአዳማ ከተማ አሰልጣኝ ራሳቸውን ከኃላፊነት ማንሳታቸውን አስታወቁ
አዲስ አበባ ፣ የካቲት 16፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) የአዳማ ከተማ አሰልጣኝ አስቻለው ኃይለሚካኤል ራሳቸውን ከኃላፊነት ማግለላቸውን አስታወቁ፡፡
አዳማ ከተማ ዛሬ ረፋድ ላይ በባህርዳር ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ በኢትዮጵያ ቡና የ4 ለ 1 ሽንፈት አስተናግዷል፡፡
አሰልጣኝ አስቻለው ኃይለሚካኤል የጨዋታውን መጠናቀቅ ተከትሎ በሰጡት አስተያየትም በገዛ ፍቃዳቸው ራሳቸውን…