Fana: At a Speed of Life!

ስፓርት

ክርስቲያኖ ሮናልዶ የማንቼስተር ዩናይትድ ዝውውሩን አጠናቀቀ

አዲስ አበባ ፣ ነሐሴ 25 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) ክርስቲያኖ ሮናልዶ የማንቼስተር ዩናይትድ ዝውውሩን አጠናቀቀ። ፖርቹጋላዊው የፊት መስመር ተጫዋች የላንክሻየሩን ክለብ በይፋ የተቀላቀለ ሲሆን፥ ለዝውውሩም 19 ነጥብ 8 ሚሊየን ፓውንድ ክፍያ በክለቦቹ መካከል ስምምነት ተደርሷል። ከዚህ ውስጥ 12 ነጥብ 9 ሚሊየን ፓውንዱ በቀጥታ የሚከፈል ሲሆን፥ ቀሪው ገንዘብ በቆይታው እየታየ የሚጨመር መሆኑን የደይሊ ሜይል ዘገባ ያመላክታል። ሮናልዶ ዳግም በተቀላቀለው የቀድሞ ክለቡ በሳምንት 385 ሺህ ፓውንድ ክፍያ የሚያገኝ ሲሆን፥ ለአንድ አመት…
Read More...

ጠ/ሚ ዐቢይ የዓለም ግማሽ ማራቶን ክብረ ወሰን ለሰበረችው አትሌት ያለምዘርፍ የእንኳን ደስ አለሽ መልዕክት አስተላለፉ

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 24፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ የዓለም ግማሽ ማራቶን ክብረወሰንን ለሰበረችው አትሌት ያለምዘርፍ የኋላው የእንኳን ደስ ያለሽ መልዕክት አስተላልፈዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ "የኢትዮጵያ ልጅ አትሌት ያለምዘርፍ የኋላው በሴቶች ግማሽ ማራቶን ሩጫ የዓለም ክብረ ወሰን ባለቤት በመሆኗ ኮርተናል፤እንኳን ደስ ያለሽ"ብለዋል። "እንዲህ…

የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን የኡጋንዳ አቻውን 2 ለ 1 አሸነፈ

አዲስ አበባ ፣ ነሐሴ 23፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) ኢትዮጵያ እና ኡጋንዳ ባካሄዱት የወዳጅነት እግር ኳስ ጨዋታ ኢትዮጵያ 2 ለ 1 በሆነ ውጤት አሸንፋለች፡፡   ለኢትዮጵያ የማሸነፊያ ግቦችን አቡበከር ናስር 11ኛው ደቂቃ እንዲሁም አቤል ያለው 54ኛው ደቂቃ ላይ አስቆጥረዋል፡፡   ኡጋንዳን ከሽንፈት ያልታደገቻትን ብቸኛ ጎል ደግሞ የኑስ ሰንታሙ 56ኛው…

አትሌት ያለምዘርፍ በሴቶች ግማሽ ማራቶን ሩጫ ክበረ ወሰን ሰበረች

አዲስ አበባ ፣ ነሐሴ 23፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) ኢትዮጵያዊቷ አትሌት ያለምዘርፍ የኋላው በአየርላንድ አንትሪም ኮስት በተካሄደው የሴቶች ግማሽ ማራቶን ሩጫ የዓለም ክበረ ወሰን ሰብራለች።   አትሌት ያለምዘርፍ 1:03.43 በሆነ ሰዓት በመግባት ነው የርቀቱን ክብረ ወሰን መያዝ ያቻለችው፡፡   በዚህም ከዚህ በፊት በኬኒያዊቷ አትሌት ሩት…

ፌዴሬሽኑ በአረንጓዴ አሻራ የንቅናቄ መርሃ ግብር ላይ ተሳተፈ

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 22፣ 2013(ኤፍ ቢ ሲ) በግብርና ሚኒስቴር በተጠራው "ኑ ኢትዮጵያን አረንጓዴ እናልብሳት" በሚል መሪ ቃል የሚከናወን የንቅናቄ መርሃ ግብር ላይ የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ተሳታፊ ሆኗል፡፡ በፌዴሬሽኑ ፕሬዚዳንት ኮማንደር አትሌት ደራርቱ ቱሉ የተመራው የስራ አስፈፃሚና ማኔጅመንት ኮሚቴ አባላት፣ እንዲሁም ታዋቂ አትሌቶችና አሰልጣኞችን የያዘ ልኡክ…

ኤቨርተንና ሌስተር ሲቲ ተጋጣሚዎቻቸውን አሸነፉ

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 22፣ 2013(ኤፍ ቢ ሲ)ዛሬ 11 ሰዓት ላይ በተደረጉ አምስት የእንግሊዝ ፕሪምየር ሊግ ጨዋታዎች ሁለቱ በመሸናነፍ ሲጠናቀቁ ሶስቱ ደግሞ በአቻ ውጤት ተጠናቀዋል፡፡ በዚህም መሰረት ኤቨርተንና ሌስተር ሲቲ ተጋጣሚዎቻቸውን ሲያሸንፉ÷ አስቶንቪላ ከብሬንት ፎርድ፣ ኒውካስል ዩናትድ ከሳውዝ ሃምፕተን፣ ዌስትሃም ዩናትድ ከክሪስታል ፓላስ አቻ ተለያይተዋል፡፡…

ማንችስተር ሲቲ አርሰናልን በሰፊ ውጤት አሸነፈ

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 22፣ 2013(ኤፍ ቢ ሲ) ዛሬ በተካሄደው የእንግሊዝ ፕሪምየር ሊግ ጨዋታ ማንችስተር ሲቲ አርሰናልን 5ለ0 በሆነ ሰፊ ውጤት አሸንፏል፡፡ ለማንችስተር ሲቲ ኤልካይ ጉንዶጋን በ7ኛው ደቂቃ፣ ፌራን ቶሬዝ በ12ኛው እና በ84ኛው ፣ ገብርኤል ጄሱስ በ43ኛው እና ሮድሪጎ ሄርናንዴዝ በ53ኛው ደቂቃ ጎሎቹን አስቆጥረዋል፡፡ በጨዋታው የአርሰናል የመሃል ሜዳ…