ስፓርት
የሴካፋ ውድድር በባህር ዳር ዓለም አቀፍ ስታዲየም ሊካሄድ ነው
አዲስ አበባ ፣ ሰኔ 18 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) ከ 23 ዓመት በታች የምስራቅና መካከለኛ አፍሪካ ዋንጫ ውድድር በኢትዮጵያ አስተናጋጅነት በባህር ዳር ከተማ ይካሄዳል፡፡
ጨዋታው ከሰኔ 26 እስከ ሀምሌ 11 ቀን 2013 ዓ.ም የሚካሄድ ሲሆን 11 የምስራቅና መካከለኛ አፍሪካ ሀገሮች እና አንድ ተጋባዥ ሀገር በድምሩ 12 አገሮች የሚካፈሉበትን አህጉር አቀፍ ጨዋታ መሆኑ ተገልጿል፡፡
የኢትዮጵያ ከ23 ዓመት በታች ብሔራዊ ቡድንም ቅድመ ዝግጅቱን አጠናቆ በትናንትናው እለት ባህርዳር ከተማ ገብቷል፡፡…
Read More...
የአትሌት አበበ ቢቂላ እና የአትሌት ዋሚ ቢራቱን የኦሳካ ማራቶን ድል ለመዘከር በብሄራዊ ቤተመንግስት የችግኝ ተከላ ተካሄደ
አዲስ አበባ ፣ ሰኔ 18 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ)አትሌት አበበ ቢቂላ እና አትሌት ዋሚ ቢራቱ በኦሳካ የማራቶን ውድድር ድል የተቀዳጁበትን 60ኛ ዓመት ምክንያት በማድረግ በብሄራዊ ቤተመንግስት የችግኝ ተከላ ተካሂዷል።
አትሌት ዋሚ ቢራቱና በኢትዮጵያ የጃፓን አምባሳደር ኢቶ ታካኮ በጋራ በመሆን ችግኝ ተክለዋል።
አምባሳደሯ ከአንድ ወር በኋላ በሚካሄደው የቶኪዮ ኦሎምፒክ…
በትግራይ ክልል ሲካሄድ የቆየው የብቃት ምዝና አትሌቲክስ ውድድር ተጠናቀቀ
አዲስ አበባ ፣ ሰኔ 15 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ)በትግራይ ክልል ለአንድ ሳምንት ያህል ሲካሄድ የቆየው የብቃት ምዘና የአትሌቲክስ ውድድር ተጠናቀቀ።
የክልሉ ጊዜያዊ አስተዳደር አትሌትክስ ፌዴሬሽን ጽህፈት ቤት ፀሐፊ አቶ ጌታቸው ማሞ ÷በክልሉ በነበረው ችግር ለሰባት ወራት ያህል ተቋርጦ የቆየውን የአትሌቲክስ ውድድር ማስቀጠል ተችሏል።
በዚህም በትግራይ አለም አቀፍ…
በአውሮፓ ዋንጫ በምድብ 1 ዌልስ ጥሎ ማለፉን ተቀላቀለች
አዲስ አበባ ፣ ሰኔ 14 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) በአውሮፓ ዋንጫ በምድብ 1 ዌልስ ጥሎ ማለፉን መቀላቀሏን አረጋግጣለች፡፡
ትናንት ምሽት ከጣሊያን ጋር የተጫወቱት ዌልሶች 1 ለ 0 ቢሸነፉም ጥሎ ማለፉን መቀላቀላቸውን አረጋግጠዋል፡፡
ጣሊያን ጨዋታውን ፔሲና ባስቆጠራት ጎል 1 ለ 0 አሸንፋለች፡፡
ውጤቱን ተከትሎም ጣሊያን ምድቡን 9 ነጥብ በመያዝ ስትጨርስ ዌልስ በ4…
በአውሮፓ ዋንጫ ፈረንሳይ ከሃንጋሪ አቻ ተለያዩ
አዲስ አበባ ፣ ሰኔ 12 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) በአውሮፓ ዋንጫ የምድብ 6 አንድ ጨዋታ ተካሄዷል፡፡
ሃንጋሪን ከፈረንሳይ ያገናኘው ጨዋታ አንድ አቻ በሆነ ውጤት ተጠናቋል፡፡
ሃንጋሪ በፊዮላ ጎል ጨዋታውን መምራት ብትችልም አንቷን ግሪዝማን ለፈረንሳይ የአቻነቷን ጎል አስቆጥሮ ጨዋታው 1 ለ 1 በሆነ ውጤት ፍጻሜውን አግኝቷል፡፡
ውጤቱን ተከትሎም ፈረንሳይ ምድቡን…
ኢትዮ አፍሪካ የአሰግድ ተስፋዬ የመታሰቢያ ውድድር አሸናፊ ሆነ
አዲስ አበባ ፣ ሰኔ 12 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) የአሰግድ ተስፋዬ የመታሰቢያ ውድድር በኢትዮ አፍሪካ የእግር ኳስ ቡድን አሸናፊነት ተጠናቀቀ፡፡
የፍጻሜ ጨዋታው በኢትዮ አፍሪካ እና አበበ ቢቂላ ቡድኖች መካከል የተደረገ ሲሆን፥ መደበኛ የጨዋታ ክፍለ ጊዜው አንድ ተጠናቋል፡፡
በመለያ ፍጹም ቅጣት ምት ኢትዮ አፍሪካ 5 ለ 4 አሸናፊ ሆኗል።
ውድድሩ መጠናቀቁን…
በአውሮፓ ዋንጫ የምድብ ጨዋታ ስዊድን ስሎቫኪያን 1ለ 0 አሸነፈች
አዲስ አበባ ፣ ሰኔ 11 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) ከጥቂት ደቂቃዎች በፊት በተጠናቀቀው የአውሮፓ ዋንጫ የምድብ ጨዋታ ስዊድን ስሎቫኪያን 1ለ0 አሸንፋለች፡፡
ስዊዲንን አሸናፊ ያደረገችውን ጎል ኤሚል ፎርስበርግ በ77ኛው ደቂቃ በፍጹም ቅጣት ምት አስቆጥሯል፡፡
ስዊድን የዛሬውን ጨዋታ ማሻነፏን ተከትሎ ወደቀጣዩ ዙር የማለፍ ዕድሏን አስፍታለች፡፡
ወቅታዊ፣ትኩስ እና…