Fana: At a Speed of Life!

ስፓርት

በዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና በ800 ሜትር ሴቶች አትሌት አያል የወርቅ ሜዳልያ አሸነፈች

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 15፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) በዓለም ከ20 ዓመት በታች አትሌቲክስ ሻምፒዮና በ800 ሜትር ሴቶች ውድድር አትሌት አያል ዳኛቸው የወርቅ ሜዳልያ አሸነፈች፡፡ በኬንያ ናይሮቢ እየተካሄደ በሚገኘው የዓለም ከ20 ዓመት በታች አትሌቲክስ ሻምፒዮና በ800 ሜትር ሴቶች ውድድር ለኢትዮጵያ ሁለተኛው የወርቅ ሜዳልያ በመሆን ተመዝግቧል፡፡ አትሌት አያል ዳኛቸው በ2:02.96 በሆነ ሰዓት 1ኛ በመውጣት የወርቅ ሜዳልያ ለሀገሯ አስመዝግባለች። በሌላ በኩል በ1500 ሜትር ወንዶች ውድድር የተሳተፋት አትሌት ወገኔ ሰብስቤ…
Read More...

ዋልያዎቹ የመጀመሪያ የምድብ ማጣሪያ ጨዋታቸውን ነሐሴ 28 ያከናውናሉ

አዲስ አበባ ፣ ነሐሴ 15 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን የአለም ዋንጫ ማጣሪያ ጨዋታዎችን የሚያደርግባቸው ቀናት ታውቀዋል። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን በኳታር አስተናጋጅነት ለሚካሄደው 2022 የዓለም ዋንጫ ማጣሪያ በምድብ 7 ከጋና፣ዚምቧቡዌ እና ደቡብ አፍሪካ ጋር መደልደሉ ይታወቃል። ዋልያዎቹ የመጀመሪያ የምድብ ማጣሪያ ጨዋታቸውን…

የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን የሚያደርገውን ዝግጅት እንደቀጠለ ነው

አዲስ አበባ ፣ ነሐሴ 14 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) በአሰልጣኝ ውበቱ አባተ የሚመራው የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን የሚያደርገውን ዝግጅት እንደቀጠለ ነው። ቡድኑ ትናንት በአዳማ አበበ ቢቂላ ስታዲየም እንዲሁም ዛሬ ረፋድ በአዳማ ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርስቲ ሜዳ ልምምድ መስራቱን የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን መረጃ ያመላክታል። አጥቂው አቡበከር ናስርና ሱራፌል ዳኛቸውም…

ከ20 ዓመት በታች የዓለም የአትሌቲክስ ሻምፒዮና ኢትዮጵያ በ3 ሺህ ሜትር የሴቶች ውድድር የነሀስ ሜዳሊያ አገኘች

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 13፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) በኬንያ  እየተካሄደ ባለው 18ኛው ከ20 ዓመት በታች የዓለም የአትሌቲክስ ሻምፒዮና ኢትዮጵያ በ3 ሺህ ሜትር የሴቶች ውድድር  የነሀስ ሜዳሊያ  አገኘች። ከጥቂት ደቂቃዎች በፊት ፍፃሜውን ባገኘው የሴቶች 3ሺህ ሜትር ውድድር ኢትዮጵያን በብቸኝነት የወከለችው አትሌት መልክናት ውዱ  የነሀስ ሜዳሊያ ማግኘቷን ከአትሌቲክስ ፌዴሬሽን…

ኢትዮጵያ በ5 ሺህ ሜትር የወንዶች ውድድር የብር ሜዳሊያ አገኘች

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 13፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) በኬንያ ናይሮቢ እየተካሄደ ባለው 18ኛው ከ20 ዓመት በታች የዓለም የአትሌቲክስ ሻምፒዮና ኢትዮጵያ በ5 ሺህ ሜትር የወንዶች ውድድር የብር ሜዳሊያ አግኝታለች። ለኢትዮጵያ የብር ሜዳሊያውን በአትሌት ታደሰ ወርቁ አማካኝነት ያገኘች ሲሆን በሌላኛው ኢትዮጵያዊ አትሌት አዲሱ ይሁኔ 4ተኛ ደረጃ ማግኘቷን ከአትሌቲክስ…

ዛሬ በሚካሄዱ የፍጻሜ ውድድሮች ኢትዮጵያውያን አትሌቶች ይጠበቃሉ

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 13፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) በኬንያ ናይሮቢ እየተካሄደ በሚገኘው 18ኛው የዓለም ከ20 ዓመት በታች አትሌቲክስ ሻምፒዮና ዛሬ በሁለተኛ ቀን ውሎው ኢዮጵያውያን አትሌቶች የሚሳተፉባቸው የፍጻሜ ውድድሮች ይጠበቃሉ፡፡ በዚህም በ5000 ሜትር አዲሱ ይሁኔ እና መብራቱ ወርቅነህ የሚሳተፉበት የፍጻሜ ውድድር ከቀኑ 10፡30 እደሚካሄድ የወጣው መርሃ ግብር…

አትሌት ታደሰ ወርቁ የወርቅ ሜዳሊያ አሸናፊ ሆነ

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 12፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) በናይሮቢ እየተካሄደ ባለው የዓለም ከ20 ዓት በታች ወጣቶች አትሌቲክስ ሻምፒዮና ኢትዮጵያ በ3000ሜ የወንዶች ሩጫ የወርቅና የብር ሜዳሊያዎችን አሸነፈች፡፡ በውድድሩ ኢትዮጵያን የወከሉት አትሌት ታደሰ ወርቁ እና አትሌት አሊ አብዱልመናን ሜዳሊያዎቹን አስገኝተዋል። በዚህም አትሌት ታደሰ ወርቁ 7:42:09…