Fana: At a Speed of Life!

ስፓርት

የአርባምንጭ ከተማ እግር ኳስ ቡድን 4 ሚሊየን ብር የማበረታቻ ሽልማት ተበረከተለት

አዲስ አበባ ፣ ሚያዝያ 23፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) አርባምንጭ ከተማ እግር ኳስ ቡድን ወደ ፕሪሚየር ሊግ በመግባቱ ከክልሉ መንግስት የማበረታቻ ሽልማት ተበረከተለት። ቡድኑ ቀሪ ጨዋታዎች እያሉት ከምድቡ አንደኛ በመሆን ፕሪሚየር ሊጉን መቀላቀል ችሏል። ይህንን ተከትሎም የክልሉ መንግስት ለቡድኑ የ4 ሚሊየን ብር የማበረታቻ ሽልማት ማበርከቱን እንዲሁም አሁን በፕሪሚየር ሊጉ እየተሳተፉ ለሚገኙት ሀዲያ ሆሳዕና ፣ ወላይታ ዲቻና ወልቂጤ ከተማ እግር ኳስ ቡድኖችም ለእያንዳዳቸው የ2 ሚሊየን ብር የማበረታቻ ስጦታ ማበርከቱን በደቡብ ክልል…
Read More...

በፕሪሚየር ሊጉ ኢትዮጵያ ቡና ከጅማ አባ ጅፋር አቻ ተለያይተዋል

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 20፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) በቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ  ኢትዮጵያ ቡና ከጅማ አባ ጅፋር ያለምንም ግብ 0 ለ 0 በሆነ አቻ ውጤት ተለያይተዋል። በጨዋታው ኢትዮጵያ ቡናዎች ከተከተያዮቻቸው እና ከመሪው ፋሲል ከነማ ያላቸውን የነጥብ ልዩነት ለማጥበብ የነበራቸውን እድል ሳይጠቀሙበት ቀርተዋል። ውጤቱን ተከትሎም ኢትዮጵያ ቡና በ34 ነጥብ…

በፕረሚየር ሊጉ ወላይታ ዲቻ ቅዱስ ጊዮርጊስን በማሸነፍ ደረጃውን አሻሻለ

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 20፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) በቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ወላይታ ዲቻ ከዱስ ጊዮርጊስን በማሸነፍ ደረጃውን አሻሻለ። ወላይታ ዲቻ ቅዱስ ጊዮርጊስን 2 ለ 1 በማሸነፍ በ28 ነጥብ በደረጃ ሰንጠረዡ 6ኛ ደረጃ ሲቀመጥ ቅዱስ ጊዮርጊስ ባለበት ለመቆየት ተገዷል። ስንታየሁ መንግስቱ ለወላይታ ዲቻ በጨዋታና በፍፁም ቅጣት ምት ያስቆጠረ ሲሆን ቅዱስ…

ፋሲል ከነማ ዋንጫውን ለማንሳት ተቃርቧል

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 19፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) በ21ኛው ሳምንት የቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ፋሲል ከነማ ዋንጫውን ለማንሳት ተቃርቧል፡፡ ዛሬ በተካሄደው ጨዋታም አዳማ ከተማን 2 ለ 1 በሆነ ውጤት አሸንፏል፡፡ ለፋሲል ከነማ የማሸነፊያ ግቦቹን ሙጂብ ቃሲም እና በዛብህ መለዮ አስቆጥሯል፡፡ የአዳማ ከተማን ብቸኛ ግብ ደግሞ ሰይፈ ዛኪር አስቆጥሯል፡፡…

ፌዴሬሽኑ ለአፍሪካ ዋንጫ ላለፉት ዋልያዎቹ 6 ሚሊየን ብር ሽልማት ለማበርከት ወሰነ

አዲስ አበባ ፣ ሚያዝያ 19 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ስራ አስፈጻሚ ኮሚቴ  ከ8 ዓመት በኋላ ወደ አፍሪካ ዋንጫ ለለተመለሰው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ( ዋልያዎቹ) አባላት የ6 ሚሊየን ብር ሽልማት እንዲሰጣቸው ውሳኔ አሳለፈ። የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ስራ አስፈጻሚ ኮሚቴ የተለያዩ ውሳኔዎች ማስተላለፉን ከፌዴሬሽኑ ያገኘነው መረጃ…

በፕሪሚየር ሊጉ ሃዲያ ሆሳዕና ከድሬዳዋ አቻ ተለያይተዋል

አዲስ አበባ ፣ ሚያዝያ 18 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) በ21ኛው ሳምንት የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ምሽት አንድ ሰአት ላይ ሃዲያ ሆሳዕና ከድሬዳዋ ከተማ ተጫውተዋል፡፡ ጨዋታው ያለምንም ጎል በአቻ ውጤት ተጠናቋል፡፡ 10 ሰአት ላይ በተደረገ ጨዋታ ሰበታ ከተማ ባህር ዳር ከተማን ማሸነፉ ይታወሳል፡፡ ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡- ድረ ገጽ፦…

በፕሪሚየር ሊጉ ሰበታ ከተማ ባህር ዳር ከተማን አሸነፈ

አዲስ አበባ ፣ ሚያዝያ 18 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) በ21ኛው ሳምንት የቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ሰበታ ከተማ ባህር ዳር ከተማን 2 ለ 1 አሸነፈ፡፡ ጨዋታውን ባህር ዳር ከተማ የሰበታው ሃይለሚካኤል ራሱ ላይ ባስቆጠራት ጎል 1 ለ 0 መምራት ቢችልም ሰበታ ከተማ ከመመራት ተነስቶ ባስቆጠራቸው ጎሎች አሸንፎ ወጥቷል፡፡ ፍጹም ገብረማርያም እና ዱሬሳ ሹቢሳ ለሰበታ…