Fana: At a Speed of Life!

ስፓርት

ሲዳማ ቡና ገብረ መድህን ኃይሌን ዋና አሠልጣኝ አድርጎ ቀጠረ

አዲስ አበባ፣ የካቲት 3፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) የሲዳማ ቡና እግር ኳስ ክለብ አቶ ገብረ መድህን ኃይሌ ዋና አሠልጣኝ አድርጎ መቅጠሩን የክለቡ ሥራ አስፈፃሚ ቦርድ አስታውቋል። ክለቡ ከቀረቡት ዕጩ አሠልጣኞች ጥቆማ መካከል አሠልጣኙ ያላቸውን የረጅም ዓመታት ሥራ ልምድ፣ የሕይወት ተሞክሮ፣ በአሠልጣኝነት ዘመን ያሳዩትን ውጤታማነት ከግምት ውስጥ በማስገባት ቦርዱ ዋና አሠልጣኝ አድርጎ ቀጥሯቸዋል። አሠልጣኙ ከዚህ ቀደም ባሠለጠኗቸው ክለቦች ጅማ አባጅፋር እና መቐለ 70 አንደርታ የእግር ኳስ ክለቦች ሻምፒዮን ያደረጉ ሲሆን፤ በመከላከያ እግር…
Read More...

ጉዳፍ ፀጋይ የ1500 ሜትር የአለም ክብረወሰንን አሻሻለች

አዲስ አበባ ፣ የካቲት 3 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) ጉዳፍ ፀጋይ በሌቪን ፈረንሳይ በተካሄደ የ1500 ሜትር የቤት ውስጥ ውድድር አዲስ የአለም ክብረወሰን አስመዘገበች። አትሌቷ በፈረንጆቹ 2014 አትሌት ገንዘቤ ዲባባ በካርልስሩህ ያስመዘገበችውን ክብረወሰን በ2 ሰከንድ በማሻሻል ርቀቱን በ3:53.09 ማጠናቀቅ ችላለች። አትሌት ለምለም ሀይሉም በዚሁ የፈረንሳይ የቤት…

ጋቶች ፓኖም ወላይታ ዲቻን ለመቀላቀል ተስማማ

አዲስ አበባ ፣ የካቲት 2 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) የቀድሞው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ብድን አማካይ ተጫዋች ጋቶች ፓኖም በአሰልጣኝ ዘላለም ሽፈራው የሚሰለጥነውን ወላይታ ዲቻን ለመቀላቀል ተስማማ። ጋቶች ከግብፁ ክለብ ከሀራስ አልሁዳድ ጋር ቀሪ የውል ጊዜው ሳይቋጭ በስምምነት ከክለቡ ጋር መለያየቱ ታውቋል። ከዛ በፊት ለሌላኛው የግብፅ ፕሪሚየር ሊግ ክለብ ኤል ጉና መጫወቱ…

በፕሪሚየር ሊጉ ፋሲል ከነማ ድሬዳዋ ከተማን 2ለ0 አሸነፈ

አዲስ አበባ፣ ጥር 28፣ 2013(ኤፍ ቢ ሲ) በቤትኪንግ የኢትዮጵያ ወንዶች ፕሪሚየር ሊግ 11 ኛ ሳምንት ዛሬ ከሰዓት በተደረገ ጨዋታ ፋሲል ከነማ ድሬዳዋ ከተማን 2ለ0 አሸነፏል። ለፋሲል ከነማ የማሸነፊይ ግቦቹን በዛብህ መላዮና በረከት ደስታ አስቆጥረዋል። ረፋድ ላይ በተካሄደው ጨዋታ ወልቂጤ ከተማና ሃዋሳ ከተማ አቻ ተለያይተዋል። ፋሲል ከነማ በ10 ጨዋታዎች…

ሐድያ ሆሳዕና የዕግድ ውሳኔ ተላለፈበት

አዲስ አበባ፣ ጥር 28፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) ሐድያ ሆሳዕና የእግር ኳስ ክለብ ከዚህ በፊት የተወሰነበትን ውሳኔ ተግባራዊ ባለማድረጉ ምክንያት የዕግድ ውሳኔ ማስተላለፉን የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን አስታወቀ። የሐድያ ሆሳዕና ተጫዋች የሆነው አብዱልሰሚድ አሊ ደሞዝ አልተከፈለኝም በማለት ያቀረበውን ክስ ተከትሎ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን የዲሲፕሊን ኮሚቴ ለተጫዋቹ…

በፕሪሚየር ሊጉ ወልቂጤ ከተማ ከሃዋሳ አቻ ተለያዩ

አዲስ አበባ፣ ጥር 28፣ 2013(ኤፍ ቢ ሲ) በቤትኪንግ የኢትዮጵያ ወንዶች ፕሪሚየር ሊግ 11 ኛ ሳምንት ዛሬ ረፋድ በተደረገ ጨዋታ ወልቂጤ ከተማና ሃዋሳ ከተማ 0 ለ 0 በሆነ ውጤት ተለያይተዋል። በጨዋታው ሁለቱም ቡድኖች ግብ ማስቆጠር አልቻሉም፡፡ የሊጉ የ11ኛ ሳምንት መርሐ ግብር ጨዋታ ዛሬ 9 ሰዓትም የሚቀጥል ሲሆን ፋሲል…

በፕሪሚየር ሊጉ ሰበታ ከተማ አዳማ ከተማን አሸነፈ

አዲስ አበባ፣ ጥር 27፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) በቤትኪንግ የኢትዮጵያ ወንዶች ፕሪሚየር ሊግ 11 ኛ ሳምንት ዛሬ ከሰዓት በተደረገ ጨዋታ ሰበታ ከተማ አዳማ ከተማን 1 ለ 0 አሸንፏል። የሰበታ ከተማን የማሸነፊያ ጎል ዳዊት እስጢፋኖስ በፍጹም ቅጣት ምት አስቆጥሯል፡፡ በቤትኪንግ የኢትዮጵያ ወንዶች ፕሪሚየር ሊግ 11 ኛ ሳምንት ዛሬ…