Fana: At a Speed of Life!

ስፓርት

የኢትዮጵያውያን አትሌቶች የአለም ሻምፒዮና ማጣሪያ በስፔን ይደረጋል-ኮማንደር ስለሺ ስህን

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 4፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በ10 ሺህ ሜትር ኢትዮጵያን በዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና ለመወከል በስፔን ማላጋ የማጣሪያ ውድድር እንደሚደረግ የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌደሬሽን አስታውቋል፡፡ የፌዴሬሽኑፕሬዚዳንት ኮማንደር ስለሺ ስህን ለፋና ሚዲያ ኮርፖሬሽን እንዳሉት÷ ከ10 ሺህ ሜትር ውጪ ባሉ ርቀቶች አትሌቶች በሀገር ውስጥ በሚደረገው የኢትዮጵያ ሻምፒዮና ይመረጣሉ፡፡ ለዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና የ10 ሺህ ሜትር ማጣሪያ ከዚህ ቀደም በተመሳሳይ በስፔን ማላጋ መደረጉ የሚታወስ ነው። የዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና…
Read More...

ባህር ዳር ከተማ ኢትዮጵያ ቡናን አሸነፈ

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 2፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በ24ኛው ሣምንት የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ጨዋታ ባሕር ዳር ከተማ ኢትዮጵያ ቡናን 2 ለ 0 በሆነ ውጤት አሸንፏል። አመሻሽ 12 ሠዓት ላይ በተደረገው ጨዋታ የባህር ዳር ከተማ ማሸነፊያ ግቦችን ቸርነት ጉግሳ እና ፍፁም አለሙ ማስቆጠር ችለዋል። ውጤቱን ተከትሎ ባሕር ዳር ከተማ በ37 ነጥብ ሁለተኛ ደረጃ ላይ ሲቀመጥ÷…

ኢትዮ ኤሌክትሪክና ሀዋሳ ከተማ አቻ ተለያዩ

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 1፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በ24ኛ ሳምንት የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር ኢትዮ ኤሌክትሪክ እና ሀዋሳ ከተማ 1 ለ 1 በሆነ አቻ ውጤት ተለያይተዋል፡፡ የኢትዮ ኤሌክትሪክን ግብ አቤል ሃብታሙ ሲያስቆጥር÷ አሊ ሱሌማን ደግሞ የሀዋሳ ከተማን የአቻነት ግብ በፍጹም ቅጣት ምት ከመረብ አሳርፏል፡፡ ውጤቱን ተከትሎ ኢትዮ ኤሌክትሪክ በ29 ነጥብ…

በአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ ባርሴሎና ከቦርሲያ ዶርትሙንድ የሚያደርጉት ጨዋታ ይጠበቃል

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 1፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ የሩብ ፍፃሜ የመጀመሪያ ዙር ጨዋታዎች ቀጥለው ሲደረጉ ባርሴሎና ከቦርሲያ ዶርትሙንድ እንዲሁም ፒኤስጂ ከአስቶንቪላ ጨዋታቸውን ያደርጋሉ። የካታላኑ ክለብ ባርሴሎና ምሽት 4 ሠዓት ላይ በሜዳው የጀርመኑን ክለብ ቦርሲያ ዶርትሙንድን ያስተናግዳል። በሀንሲ ፍሊክ የሚመራው ባርሴሎና በጥሎ ማለፉ ጨዋታ…

ተጠባቂው የአርሰናል እና ሪያል ማድሪድ ፍልሚያ

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 30፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ የሩብ ፍፃሜ የመጀሪያ ዙር ጨዋታዎች ዛሬ ምሽት መደረግ ሲጀምሩ አርሰናል በኤምሬትስ ስታዲየም ምሽት 4 ሠዓት ላይ ሪያል ማድሪድን ያስተናግዳል፡፡ በጥሎ ማለፉ ጨዋታ አርሰናል ፒኤስቪን፤ ሪያል ማድሪድ ደግሞ አትሌቲኮ ማድሪድን አሸንፈው ለሩብ ፍፃሜ መድረሳቸው ይታወቃል። በየሊጋቸው ሁለተኛ ደረጃ…

ፋሲል ከነማ ቅዱስ ጊዮርጊስን አሸነፈ

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 29፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በ24ኛ ሳምንት የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ጨዋታ ፋሲል ከነማ ቅዱስ ጊዮርጊስን 2 ለ 1 በሆነ ውጤት አሸንፏል፡፡ የፋሲል ከነማን የማሸነፊያ ሁለት ግቦች ጌታነህ ከበደ ሲያስቆጥር፤ የቅዱስ ጊዮርጊስን ብቸኛ ግብ አብርሃም ጌታቸው ከመረብ አሳርፏል፡፡ ፋሲል ከነማ ተከታታይ ሦስተኛ ድሉን በሊጉ ሲያሳካ፤ ቅዱስ ጊዮርጊስ…