ስፓርት
ሚሲዮኑና ዳያስፖራው ለኦሊምፒክ ቡድን አስፈላጊውን የሞራል ድጋፍ ጋር ያደርጋል ተባለ
አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 18፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በፈረንሳይ የኢትዮጵያ ሚሲዮን እና ዳያስፖራው ለኢትዮጵያ ኦሊምፒክ ቡድን አስፈላጊውን የሞራል ድጋፍ ጋር ያደርጋል ተባለ።
በ33ኛው የፓሪስ ኦሊምፒክ የሚሳተፈው የመጀመሪያው ዙር የኢትዮጵያ ኦሊምፒክ ቡድን ፓሪስ ከተማ ገብቷል፡፡
40 አባላት ያሉት የኢትዮጵያ የኦሊምፒክ ልዑክ ዛሬ ማለዳ ፈረንሳይ ፓሪስ ሲገባ በፈረንሳይ የኢፌዴሪ ሚሲዮን እና ፈረንሳይ በሚገኙ ኢትዮጵያውያን ደማቅ አቀባበል ተደርጎለታል።
በመጀመሪያው ዙር ወደ ፓሪስ ያቀናው የኦሎምፒክ ቡድኑ በኦሊምፒክና በፓራሊምፒክ ውድድር…
Read More...
የካፍ የሴቶች ሻምፒየንስ ሊግ የሴካፋ ዞን የማጣሪያ ውድድር የምድብ ድልድል ይፋ ሆነ
አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 17፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የካፍ የሴቶች ሻምፒየንስ ሊግ የ2023 የሴካፋ ዞን የማጣሪያ ውድድር የምድብ ድልድል ይፋ መሆኑን የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌደሬሽን አስታወቀ፡፡
በዚሁ መሠረት÷ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከኬንያ ፖሊስ ቡሌትስ፣ ዬ ጆይንት፣ ዋሪየርስ ኩዊንስ እና ራየን ስፖርት ውሜንስ ጋር በምድብ አንድ ተደልድሏል፡፡
እንዲሁም ሲምባ ኩዊንስ፣…
በፓሪስ ኦሊምፒክ የሚሳተፈው የኢትዮጵያ ልዑካን ቡድን ሽኝት እየተደረገለት ነው
አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 15፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በፓሪስ በሚካሄደው 33ኛው የኦሊምፒክ ጨዋታዎች የሚሳተፈው የኢትዮጵያ ልዑካን ቡድን በብሔራዊ ቤተ-መንግስት ሽኝት እየተደረገለት ይገኛል።
በሽኝት መርሐ ግብሩ ላይ ፕሬዚዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ፣ የፌዴሬሽን ምክር ቤት አፈ ጉባኤ አገኘሁ ተሻገር፣ የባህልና ስፖርት ሚኒስትር ሸዊት ሻንካ፣ የኢትዮጵያ ኦሊምፒክ ኮሚቴ ፕሬዚዳንት…
ለመቻል ስፖርት ክለብ 1 ቢሊየን ብር መሰብሰቡ ተገለጸ
አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 15፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በ"መቻል ለኢትዮጵያ" ንቅናቄ ለመቻል ስፖርት ክለብ 1 ቢሊየን ብር መሰብሰቡ ተገለጸ፡፡
ለንቅናቄው ከታቀደው መርሐ ግብር 99 በመቶው የሚሆነውን ማሳካት እንደተቻለም ተጠቁሟል።
የመቻል ስፖርት ክለብ ቦርድ ሰብሳቢ ሰይፈ ጌታሁን (ዶ/ር) ÷የመቻል ለኢትዮጵያ ንቅናቄ በታቀደለት መርሐ-ግብር መካሄዱን አውስተው…
የባህልና ስፖርት ሚኒስትር ሸዊት ሻንካ በፓሪስ ኦሎምፒክ የሚሳተፉ አትሌቶችን አበረታቱ
አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 15፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የባህልና ስፖርት ሚኒስትር ሸዊት ሻንካ በፓሪስ ኦሎምፒክ የሚሳተፉ አትሌቶችን ልምምድ በሚያደርጉበት የኢትዮጵያ ስፖርት አካዳሚ በመገኘት ጎብኝተዋል፡፡
ወ/ሮ ሸዊት ሻንካ በዚህ ወቅት እንዳሉት÷የኢትዮጵያ አትሌቶች የሚታወቁት በዓለም አደባባይ መድረክ በአሸናፊነት ነው፡፡
ስለሆነም በኦሎምፒኩ የምትሳተፉ አትሌቶች…
የ21ኛው ክፍለ ዘመን ምርጥ አፍሪካዊ ስፖርተኛ በመባሌ ትልቅ ክብር እና ምስጋና አለኝ-አትሌት ቀነኒሳ በቀለ
አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 13፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ)በኢ ኤ ስ ፒ ኤን የ21ኛው ክፍለ ዘመን ምርጥ አፍሪካዊ ስፖርተኛ በመባሌ ትልቅ ክብር እና ምስጋና አለኝ ሲል አትሌት ቀነኒሳ በቀለ ገለፀ፡፡
ኢ ኤ ስ ፒ ኤን የ21ኛው ክፍለ ዘመን ምርጥ 10 ታላላቅ አፍሪካውያን ስፖርተኞችን ይፋ አድርጓል፡፡
በዚህም የረጅም ርቀት ሯጩ አትሌት ቀነኒሳም ቀዳሚውን ደረጃ ይዟል፡፡
ይህን…
አትሌት ቀነኒሳ በቀለ የ21ኛው ክፍለ ዘመን ምርጥ አፍሪካዊ ስፖርተኛ ተባለ
አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 13፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) አትሌት ቀነኒሳ በቀለ የ21ኛው ክፍለ ዘመን ምርጥ አፍሪካዊ ስፖርተኛ ተብሎ መመረጡን የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌደሬሽን አስታውቋል፡፡
ኢ ኤ ስ ፒ ኤን የ21ኛው ክፍለ ዘመን ምርጥ 10 ታላላቅ አፍሪካውያን ስፖርተኞችን ይፋ ማድረጉን የገለጸው ፌደሬሽኑ÷ በዚህም ኢትዮጵያ እና ኬንያ ሁለት አትሌቶችን በማስመረጥ ቀዳሚ ሆነዋል…